የሰኔ 4 ሥንክሳር#ቅድስት ሶፍያ ተጋዳሊት#ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ#ቅዱስ ሳኑሲ#አርቃድዮስና ባልንጀሮቹ #ቅዱስ አሞን

ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ 4 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ አራት በዚች ቀን በልኪም ከሚባል አገር ሳኑሲ በሰማዕትነት ሞተ ። ይህ ቅዱስ በልጅነቱ የአባቱን በጎች ሲጠብቅ ምሳውን ለእረኞች ሰጥቶ እርሱ ሁልጊዜ እስከ ማታ ይጾም ነበር ዘመዶቹም የሚሠራውን አያውቁም ነበር ። የታመሙ በሽተኞችንም ይጐበኛቸው ነበር ። በአንዲት ሌሊትም የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ ሳኑሲ ሆይ የክብርአክሊልን ትቀበል ዘንድ ተነሥተህ ወደ መኰንኑ ሒድ ክብር ይግባውና በፈጣሪህ ክርስቶስ በመኰንኑ ፊት ታመን አለው ። በነቃም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ እንደተገለጸለትና እንዳዘዘው ለእናቱ ነገራት እርሷም አዘነች አለቀሰችም ነገር ግን ትከለክለው ዘንድ አልተቻላትም ። ከዚህ በኋላ ስብራ በሚባል አገር ስሟ ማርያ የሚባል ድኆችንና መጻተኞችን የምትቀበልና የምትመግባቸው የተቀደሰች ሴት እንዳለች ስለርሷ ሰምቶ ወደርሷ ሔደ ። በሰማዕትነትም ይሞቱ ዘንድ ከርሷ ጋራ ተስማማ ። አርሳኖስ ወደ ሚባልም መኰንን በአንድነት ሔዱ በምስር ወደብ በመርከብ ውስጥ ሁኖ አገኙትና እኛ ክርስቲያኖች ነን ብለው በፊቱ በግልጥ ጮኹ በየራሱ በሆነ ሥቃይም እንዲአሠቃዩአቸው አዘዘ ቅድስት ማርያም በሥቃዩ ውስጥ ሳለች ነፍሷን አሳልፋ ሰጠች የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለች ። ቅዱስ ሳሉሲ ግን ክብር ይግባውና በላዩ በአደረው በጌታችን በኢየሱስ ኃይል የሚታገሥና የሚጸና ሆነ ። መኰንኑም ማሠቃየቱን በሰለቸው ጊዜ ወደ እንዴናው መኰንን ከብዙዎች እሥረኞች ሰማዕታት ጋራ ላከው እርሱም ያሠቃየው ጀመረ ተረከዙንም ሠንጥቀው ገመድ አግብተው በከተማው ውስጥ እንዲጐትቱት አዘዘ ። እንዳዘዛቸውም አደረገ ግን ምንም ጉዳት አልደረሰበትም ። ሁለተኛም ሥራየኛ አመጣለትና መርዝ በተመላ ጽዋ ሥራዩን አድርጎ ጠጣ ብሎ አዘዘው ። ቅዱሱም በላዩ በመስቀል ምልክት አማትቦ ጠጣው ምንም ምን ጉዳት ሳይደርስበት ቀረ ። ከማሠቃየትም በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዘዘና የከበረች ራሱን ቆረጡት የድል አክሊልንም ተቀበለ መሠርዩም አምኖ በሰማዕትነት ሞተ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን ። በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን ። ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ በዚችም ዕለት ሐራቅሊ ከሚባል አገር ቅዱስ አባት ዮሐንስ አረፈ ። የዚህም ቅዱስ አባት ስሙ ዘካርያስ ነው እርሱም የጳንጦስና የአብልያ ሀገሮች ገዢ ነበር የእናቱም ስም ኤልሳቤጥ ነው እነርሱም ይህን የተባረከ ልጅ በተሰጡ ጊዜ ስሙን ዮሐንስ ብለው ጠሩት እርሱ ከአባቱና ከእናቱ ጀምሮ ከመጥምቀ አምላክ ዮሐንስ ጋራ በስም አንድ ሁኗልና በተግሣጽና በፈሪሀ እግዚአብሔርአሳደጉት የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትን ሂሣቦችንና ጥበቦችን ሁሉ አስተማሩት እናቱም በዘመኗ ሁሉ ከእግዚአብሔር መንገድ እንዳይወጣ ታማፅነው ነበር ። አባቱም እንዲሁ ይመክረውና ያስተምረው ነበር ። ከዚያም አባቱ ከሞተ በኋላ የሃያ ዓመት ልጅ ሲሆን መስፍን ሆነ የጳንጦስና የሐራቅሊ ሌሎችም አገሮች ሁሉ ተገዙለት ። እንዲሁም እያለ የመልአክ አምሳል ሰይጣን ታየው እንዲህም አለው አንተ ትነግሥ ዘንድ ወደ አንጾኪያ ሒደህ የንጉሥ ኑማርያኖስን ልጅ አግባ ብሎ ጌታ አዝዞሃል አለው ቅዱሱም በውኑ ይህ መልአክ ነውን ግን ከአፉ የእግዚአብሔር ስም ከሰማሁ አንጾኪያ እሔዳለሁ አለ ። ከዚህ በኋላም ወደ አንጾኪያ ከተማ ሔደ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስንም ተገናኘው ንጉሡም በአየው ጊዜ አከበረው እጅግም ወደደው ። በማግሥቱም በምሳ ላይከእርሱ ጋራ እያለ ከሃድ ድዮቅልጥያኖስ አጵሎንን ያመጡት ዘንድ አዘዘ ያንንም ጣዖት ባመጡት ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ አቃለለው ስለዚህም ሥራ ንጉሡን ረገመው ሰደበውም ። ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም ቅዱስ ዮሐንስ ያደረገውን በአየ ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ በእሥር ቤት አሠረው ። በእሥር ቤትም ሳለ ክብር ይግባውና ጌታችን በብርሃን ሠረገላ ላይ ሁኖ ታየዉ ከእርሱ ጋራም መላእክት አሉ ። ይዞም ሳመው ብዙዎች ቃል ኪዳኖችንም ሰጠው ። በማግሥቱም ንጉሡ ልኮ ከእሥር ቤት አወጣዉ ወደ ርሱም አቀረበውና ለአጵሎንና ለአርዳሚስ ስገድ አለው ቅዱሱም የሰው እጅ ለሠራው እንዴት እሰግዳለሁ አለው ንጉሡ ግን ከእርሱ ጋር መታረቅ ሽቶ ብዙ የሽንገላ ነገርን ተናገረው ። ከዚህም በኋላ ግብርን ያስገብር ዘንድ ከሹመት ጋራ ወደ ግብጽ አገር ላከው ወደ ግብጽ ገዢ ወደ ስርያቆስም ስለ ርሱ እንዲህ ሲል ጽፎ ላከ እነሆ ለዮሐንስ ዘሐራቅሊ ግብር በማስገበር የአማልክትንም ቤቶች አፍርሶ አዲስ እንዲአሠራ ከግብጽና ከኢየሩሳሌም እስከ ኢትዮጵያ ድረስ ሥልጣን ሰጥቼዋለሁ ። ቅዱሱም ይህን ምክንያት ይዞ የጣዖታትን ቤቶች አፍርሶ ተዋቸው ። በዚያም ወራት ወኰንኑ ስርያቆስ የሰማዕታትን ራስ መቆረጥን ሊያዝዝ በፍርድ አደባባይ ተቀመጠ በዚያን ጊዜ ከስዒድ ዲዮስቆሮስ ፣ ቢፋሞን ፣አሕራጋኖስ ኪሮስ፣ ዮልዮስ፣ እለእስክንድሮስ፣ ዮሴፍ ፣ይስሐቅና ፣ እስጢፋኖስ የሚሉአቸው ሰዎች መጥተው እሊህ ሁሉም እኛ ክርስቲያኞች ነን እያሉ በግልጥ ጮኹ ያን ጊዜ መኰንኑ ይዞ ያለርኅራኄ ያሠቃያቸው ጀመረ ። ቅዱስ ዮሐንስም ይህን በአየ ጊዜ የሹመቱን ሥራ ትቶ እኔ ክርስቲያን ነኝ ብሎ በግልጥ ጮኸ መኰንኑም ተቆጥቶ በእግር ብረት እንዲአሥሩትና ወደ እንድና አገር ወደ መኰንኑ አርያኖስ እንዲወስዱት አዘዘ እርሱም ስለሆነው ሁሉ መረመረው ከቃሉ መልስም የተነሣ ተቆጣ በባላ እንጨት ላይ ሰቅለው በመንኰራኲር አጣብቀው እንዲጨምቁት ከዚያም ከባላው አውርደው ሥጋው እስኪቀልጥ ሆዱ ላይና ራሱ ላይ በቀጭኔ እንዲደበድቡት አዘዘ ምድሪቱም በደሙ ተመላች ከዚያም ወደ እሥር ቤት አስገቡት ። ከጥቂት ቀኖች በኋላም በማረጃ ቢላዋ ቆዳውን ገፈው ቁስሉን በማቅ ያሹት ዘንድ ዳግመኛም አመድ ጐዝጉዘው በላዩ የእሳት ፍም ከጐኑ በታች አድርገው በላዩ እንዲአስተኙት አዘዘ እንዲሁም አደረጉበት ። ሁለተኛም በእሳት የጋሉ የብረት ችንካሮችን አምጥተው በፊቱ ላይበጀሮዎቹም ላይ እንዲያኖሩዋቸው አዘዘ እንዲህም አድርገው ከወህኒ ቤት ጨመሩት ። በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጾለት ሰላምታ ሰጥቶ አጸናው ። በማግሥቱም ከወህኒ ቤት አውጥተው በጋሉ ብረት ዘንጎች ደበደቡት ። ከዚህም በኋላ ግንባሩን ወደ ምድር ደፍተው እጆቹንና እግሮቹን ከፈረስ ጭራ ላይ በገመድ አሠሩ ። ከዚህ በኋላም ባለ ሰይፍ ወጥቶ እግሮቹንና እጆቹን ራሱንም ቆረጠ እንዲህም የምስክርነቱን ተጋድሎ ፈጽሞ የድል አክሊልን ተቀበለ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ መስተጋድል ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። ቅዱስ አርቃድዮስና ባልንጀሮቹ በዚችም ቀን የአርቃድዮስ የእኅቱ የዲሙናስያ የግብጻውያኑ የአሞኒና የሚናስ የንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ጭፍሮችም የገድላቸው ፍጻሜ ሆነ ። እሊህን ቅዱሳን በእሳት ምድጃ ውስጥ ከአባ ብሶይ ጋራ በጨመሩዋቸው ጊዜ የመላእክት አለቃ ገብርኤል መጥቶ ከነበልባሉ መካከል አወጣቸው ። ወደ ንጉሡም ደርሰው ረገሙት እንዲህም አሉት የምስክርነት ሞት ፍጻሜያችንን የማትጽፍ ከዕለት ወደ ዕለት ለምን ትከፋለህ ። ንጉሡም ሰምቶ ተቆጣ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡና ሥጋቸውን በእሳት እንዲያቃጥሉ አዘዘ እንደዚህም የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ፈጽመው የክብር አክሊልን ተቀበሉ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ዕለት በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ተጋዳይ የሆነች ቅድስት ሶፍያ አንገቷን በመቆረጥ በሰማዕትነት አረፈች ። ሊቆርጧትም ይዘዋት ሲሔዱ ክብርይግባውና ጌታችን ተገለጸላት ብዙ ቃል ኪዳኖችንም ሰጣት በማይታበል ቃሉም መታሰቢያሽን የሚያደርገውን ሁሉ በስምሽም የሚመጸውተውን የገድልሽንም መጽሐፍ የሚጽፈውን ሁሉ እቀበለዋለሁ መንግሥተ ሰማያትንም አወርሰዋለሁ አለ ። ከዚህ በኋላም አንገቷን በሰይፍ ቆረጡ በጌታችንም ዘንድ የድል አክሊልን ተቀበለች ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን ። በዚችም ዕለት የአባ አሞንና የሚናስ መታሰቢያቸው ሆነ በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። ሰኔ 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፩. ቅድስት ሶፍያ ተጋዳሊት ወሰማዕት ፪. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ ሰማዕት ፫. ቅዱስ ሳኑሲ ሰማዕት ፬.ቅድስት ማርያ ሰማዕት ፭. ቅዱስ አርቃድዮስና ባልንጀሮቹ ሰማዕታት ፮. ቅዱስ አሞን ሰማዕት ወርኀዊ በዓላት ፩.ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ወንጌላዊ ፪.ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ እንግዲህ አትፍሯቸው ። የማይገለጥ የተከደነ: የማይታወቅም የተሠወረ ምንም የለምና ። በጨለማ የምነግራችሁን በብርሃን ተናገሩ ። በጀሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ ስበኩ ። ሥጋንም የሚገድሉትን: ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ ። ይልቅስ ነፍስንም: ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ ። ማቴ 10÷26 ‪@yekidusantarik‬ ‪@swromariyamgedam‬ ‪@EOTCOrthodoxChannel1‬

الرقية الشرعية للشفاءمن السحروالعين والحسد حصن من الشيطان رقية البيت والاولاد بصوت القارئ سعيد حمدان
▶︎

الرقية الشرعية للشفاءمن السحروالعين والحسد حصن من الشيطان رقية البيت والاولاد بصوت القارئ سعيد حمدان

አትጨነቁ|| እጅግ ጥዑም ስብከት || በርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረኪዳን ግርማ Aba Gebrekidan Girma New sibket
▶︎

አትጨነቁ|| እጅግ ጥዑም ስብከት || በርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረኪዳን ግርማ Aba Gebrekidan Girma New sibket

የሰኔ 5 ሥንክሳር #ቅዱስ ያዕቆብ ምሥራቃዊ #ለባሲተ ክርስቶስ ማርታ#አባ ብሶይና ቢፋሞን#አቡዬ ጻድቁ#ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት
▶︎

የሰኔ 5 ሥንክሳር #ቅዱስ ያዕቆብ ምሥራቃዊ #ለባሲተ ክርስቶስ ማርታ#አባ ብሶይና ቢፋሞን#አቡዬ ጻድቁ#ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት

ሰይፈ ሥላሴ ጸሎትን እንዴት አንጸልይ? አስደናቂው የሰይፈ ሥላሴ ጸሎት ጥቅሞች! በሰይፈ ሥላሴ ጸሎት ዙሪያ የተሰጠ ሰፊ ማብራሪያ!
▶︎

ሰይፈ ሥላሴ ጸሎትን እንዴት አንጸልይ? አስደናቂው የሰይፈ ሥላሴ ጸሎት ጥቅሞች! በሰይፈ ሥላሴ ጸሎት ዙሪያ የተሰጠ ሰፊ ማብራሪያ!

||ሰኔ ሚካኤል || ቅዱስ ሚካኤል ይነሳል በዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ #ዜኑ_ሚዲያ_zenu_media
▶︎

||ሰኔ ሚካኤል || ቅዱስ ሚካኤል ይነሳል በዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ #ዜኑ_ሚዲያ_zenu_media

Ethiopia እለተ እሮብ ሰኔ 17/2018 ሰበር መረጃዎች #AnchorMedia #EthiopiaNews Anchor Media FanoNews #ethionation
▶︎

Ethiopia እለተ እሮብ ሰኔ 17/2018 ሰበር መረጃዎች #AnchorMedia #EthiopiaNews Anchor Media FanoNews #ethionation

🔴ለእግዚአብሔር የምስጢሩ  ገዳም አበ ምኔት
▶︎

🔴ለእግዚአብሔር የምስጢሩ ገዳም አበ ምኔት

የሰኔ 17 ሥንክሳር #አባ ለትጹን #ገሪማ ገረምከነ#አባ ጰላሞን #ቅዱሳን ጻድቃን#እንኳን ሰው እፅዋት የታዘዙለት አባት
▶︎

የሰኔ 17 ሥንክሳር #አባ ለትጹን #ገሪማ ገረምከነ#አባ ጰላሞን #ቅዱሳን ጻድቃን#እንኳን ሰው እፅዋት የታዘዙለት አባት

አጋንንት የሚባርር ፀሎት! | ድንቅ ትምህርት በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ Aba Gebrekidan New Sibket 2026
▶︎

አጋንንት የሚባርር ፀሎት! | ድንቅ ትምህርት በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ Aba Gebrekidan New Sibket 2026

ቃየን ከየት አምጥቶ ሚስት አገባ? |  መጽሐፍ ቅዱስ 66ቱ ብቻ ለሚሉ ጥያቄ  | መምህር ዘበነ ለማ
▶︎

ቃየን ከየት አምጥቶ ሚስት አገባ? | መጽሐፍ ቅዱስ 66ቱ ብቻ ለሚሉ ጥያቄ | መምህር ዘበነ ለማ

" ዝሕጉስ-ዜና" ኤርትራ ናይ ምህንድስና ህንጻ ጨረታ|ኣብ ሳዋ ትግራይ |ሚኒስተር ዜና የማነ"ሳዋ"| 24|6|2026
▶︎

" ዝሕጉስ-ዜና" ኤርትራ ናይ ምህንድስና ህንጻ ጨረታ|ኣብ ሳዋ ትግራይ |ሚኒስተር ዜና የማነ"ሳዋ"| 24|6|2026

Breaking News - ዘሐጉስ ኤርትራ ሓድሽ ዕደና - ወላዲት ፕ/ት ኢሰያስ ዓሪፈን  - ሊብያ ንኤርትራውያን ህጹጽ - FBI $100 ሚልዮን ዘታለለት ይደሊ
▶︎

Breaking News - ዘሐጉስ ኤርትራ ሓድሽ ዕደና - ወላዲት ፕ/ት ኢሰያስ ዓሪፈን - ሊብያ ንኤርትራውያን ህጹጽ - FBI $100 ሚልዮን ዘታለለት ይደሊ

የጥቅምት 14 ሥንክሳር@ቅዱስ ሙሴ መርዓዊ @ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ@ ይህንን ያውቁ ኖሯል?@ሁለት ተመሳሳይ ቅዱሳን በአንድ ቀን የሚከበሩ
▶︎

የጥቅምት 14 ሥንክሳር@ቅዱስ ሙሴ መርዓዊ @ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ@ ይህንን ያውቁ ኖሯል?@ሁለት ተመሳሳይ ቅዱሳን በአንድ ቀን የሚከበሩ

የሰኔ 13 ሥንክሳር#ቅዱስ ገብርኤል ለዳንኤል የተላከበት#አባ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም #ቃይናን #ማትያን#በወርቅ ሣህን የሚመገበው ዓይኑ ጠፋ
▶︎

የሰኔ 13 ሥንክሳር#ቅዱስ ገብርኤል ለዳንኤል የተላከበት#አባ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም #ቃይናን #ማትያን#በወርቅ ሣህን የሚመገበው ዓይኑ ጠፋ

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስዕሏ ስር ይህን አድርጉ ሀሳባችሁ ይሳካል ፣ አባ ገብረኪዳን
▶︎

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስዕሏ ስር ይህን አድርጉ ሀሳባችሁ ይሳካል ፣ አባ ገብረኪዳን

የሐዋርያት ሥራ ሙሉ ታሪክ - ክፍል 1 - መባዕ ቲቪ (Meba TV)
▶︎

የሐዋርያት ሥራ ሙሉ ታሪክ - ክፍል 1 - መባዕ ቲቪ (Meba TV)

ሰይፈ ሥላሌ መፀለይ እንዴተ ነው ? #መምህር_ተስፋዬ #የህይወት_ገጠመኝ @kesishenokweldemariam2240
▶︎

ሰይፈ ሥላሌ መፀለይ እንዴተ ነው ? #መምህር_ተስፋዬ #የህይወት_ገጠመኝ @kesishenokweldemariam2240

🔴 ክረምቱ ሳይመጣ ፈጥነህ ና || ለቤተ ክርስቲያን ችግር መፍትሔ | ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ |Aba Gebrekidan New Sibket 2026
▶︎

🔴 ክረምቱ ሳይመጣ ፈጥነህ ና || ለቤተ ክርስቲያን ችግር መፍትሔ | ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ |Aba Gebrekidan New Sibket 2026

ለማመን የሚከብድ የቅዱስ ገብርኤል ተዓምር | ከሞት ወደ ሂወት የተመለሰች ነፍስ |  ቅዱስ ገብርኤል በአንድ ቤት ሁለት ነፍሳትን አዳነ
▶︎

ለማመን የሚከብድ የቅዱስ ገብርኤል ተዓምር | ከሞት ወደ ሂወት የተመለሰች ነፍስ | ቅዱስ ገብርኤል በአንድ ቤት ሁለት ነፍሳትን አዳነ

ይህን መዝሙር 24 || በየቀኑ ከጸልያችሁ የማይሳካ ነገር የለም ||የምትፈልጉትን ሁሉ ለማግኘት እንዲህ ጸልዩ || መ/ር አድነው ወንድሙ @neamnmedia19
▶︎

ይህን መዝሙር 24 || በየቀኑ ከጸልያችሁ የማይሳካ ነገር የለም ||የምትፈልጉትን ሁሉ ለማግኘት እንዲህ ጸልዩ || መ/ር አድነው ወንድሙ @neamnmedia19