የሰኔ 5 ሥንክሳር #ቅዱስ ያዕቆብ ምሥራቃዊ #ለባሲተ ክርስቶስ ማርታ#አባ ብሶይና ቢፋሞን#አቡዬ ጻድቁ#ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት
ስንክሳር ዘወርኀ ሰኔ 5 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ አምስት በዚች ቀን ታማኝና ተጋዳይ ይሆነ ምሥራቃዊው አባት ያዕቆብ አረፈ ። ይህም ቅዱስ ከምእመን ዋልንጦስ ዘመን በኋላ የታላቁ ቈስጠንጢኖስ ልጅ በሆነ በታናሹ ቈስጠንጢኖስ ዘመንና በከሀዲው ሉልያኖስ ዘመን በምሥራቅ ካሉ ገዳማት በአንዱ ገዳም በገድል ተጠምዶ ኖረ ። ዋልንጦስ ከተገደለ በኋላም በእርሱ ፈንታ ወንድሙ ነገሠ እርሱም አርዮሳዊ ነበርየጣዖት ቤቶቻቸውን እንዲከፍቱ ሃይማኖታቸው የቀናውን የምእመናንን አብያተ ክርስቲያናትንም እንዲዘጉ አርዮሳውያንን አዘዛቸው ወደ ከፋችና ወደ ተበላሸች ሃይማኖታቸው ምእመናን በግዳጅ እስቲገቡ ድረስ እንዲሁ አደረጉ ። ይህም የንጉሡ ትእዛዝ በሚገዛው አገር ሁሉ ደረሰ ። ይህ አባ ያዕቆብም ይህን በሰማ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ፍቅር እሳትነት ልቡ ነደደ ያንጊዜም ተነሥቶ ወደ ቊስጥንጥንያ ሔደ በምዕራብ በኩል የተነሡበትን ጠላቶቹን ሒዶ ለመውጋት ሲወጣ ንጉሡን አገኘው ። ይህ አባት ያዕቆብም በፊቱ ቆሞ ንጉሥ ሆይ በጠላቶችህ ላይ እግዚአብሔር ይረዳህ ዘንድ ምእመናን እንዲጸልዩልህ አብያተ ክርስቲያናቸውን ክፈትላቸው ብዬ እለምንሃለሁ ይህን ካላደረግህ ግን እግዚአብሔር ይጥልሃል ከጠላቶችህም ሸሽተህ በእሳት ቃጠሎ ትሞታለህ አለው ። ንጉሡም ይዞ ለሚጠብቀው ወታደር በሰላምና በደኅንነት እስከምመለስ ጠብቀው ብሎ ሰጠው ። ቅዱስ ያዕቆብም አንተ በደኅና ከተመለስክ በእኔ አንደበት እግዚአብሔርአልተናገረም ማለት ነዋ አለው ። ያንጊዜም ቅዱሱን ይዘው ደብድበው አሠሩት ንጉሡም ከሠራዊቱ ጋራ ወደ ጦርነቱ ሔደ በረከሰች ጸሎታቸው አርዮሳውያን ምንም ቢራዱት ክብር ይግባውና ጌታችን በጠላቶቹ አንጻር ጣለው እነርሱም ጠላቶቹ እየተከተሉት ሸሽቶ ከአንዲት አአድ ውስጥ ገባ በዚያም በረከሰች ሃይማኖት ከሚያምኑ ወገኖቹ ጋራ በእሳት አቃጠሉት ። የቀሩትም ሠራዊት ሁሉ ሽሽተው ወደ ቊስጥንጥንያ ተመለሱ ይህንንም መልካም ዜና ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን ተናገሩ የዚህ ጻድቅ አባት ያዕቆብም ትንቢቱ ተፈጸመ ከእሥር ቤትም በክብር አስወጡት ። ምእመናንም ከሀዲያንም በላዩ መንፈስ ቅዱስ እንዳደረበት ተረዱ ከአርዮሳውያንም ብዙዎቹ የአባቶቻችን ሐዋርያት ወደሆነች ቅን ሃይማኖት ተመለሱ በዚህ አባት እግር በታች ሰግደው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በመለኮቱ ትክክል እንደሆነ ታመኑ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ዕለት የተመረጠ ኃያል ተጋዳይ አባ ብሶይ አረፈ ። የዚህ ቅዱስ አባቶቹ ክብር ይግባውና ጌታ ክርስቶስን የሚያመልኩና ትእዛዙን የሚጠብቁ ክርስቲያን ነበሩ የአባቱም ስም ታግኅስጦስ ነው እርሱም ከአንጾኪያ የቃው ገዥ ነበር የእናቱም ስም ክሪስ ይባላል ። .. ከዚህ በኋላም ሃያ ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜ የስዒድ መኰንን ወዳለበት ወደ ቃው ከተማ መጣ እርሱም ክርስቲያኖችን እያሳደደ ከእርሳቸው ይገድል ነበር ። ያን ጊዜም ክፉዎች ሰዎች ወደ መኰንኑ መጥተው ለቃልህ የማይታዘዙና ለአማልክት መስገድንም እምቢ የሚሉ ሁለት ዲያቆናት አሉ ብለው እኒህ የከበሩ አባ ብሶይንና አባ ጴጥሮስን ከሰሱአቸው ። በዚያን ጊዜም እንዲአቀርቧቸው አዘዘና አቅርበው በፊቱ አቆሙአቸው ስለ ሥራቸውም መረመራቸው ክርስቲያን እንደ ሆኑም ከቃላቸው ሰምቶ እንዲአሥሩአቸው አዘዘ ። ከሦስት ወር በኋላም የእግዚአብሔር መልአክተገልጦላቸው እኔ የምሥራች የምናገር ገብርኤል ረዳችሁና እነግራችሁ ዘንድ ወደ እናንተ እግዚአብሔር ላከኝ ስም አጠራራችሁና መታሰቢያችሁ ለዘላለሙ ይኖር ዘንድ አለውና አላቸው ። አንተም ወዳጄ ብሶይ ታላቅ ተጋድሎ አንተን ይጠብቅሃል ወደ እስክንድርያ ከተማ ሊሰዱህ አላቸው ከዚያም ወደ አንጾኪያ ወስደውህ በዚያ የምስክርነትህ ገድል ይፈጸማል ። ከዚህ በኋላም መኰንኑ ከወህኒ ቤት አውጥቶ ለጣዖት እንዲሰግድ አስገደደው እምቢ ባለውም ጊዜ ከባላ ላይ አውጥተው በግንድ ውስጥ እጅግ እንዲጨምቁት ወታደሮችን አዘዘ ። በዚያን ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ወረደ ግንዱን ሰብሮ ቅዱስ ብሶይን በመዳሠሥ አዳነው ። ከዚያም ወደ ወህኒ ቤት ጨመሩት በዚያም ብዙ በሽተኞችን ፈወሳቸው ። ዳግመኛም እንዲህ አዘዘ ከወህኒ ቤት አውጥተው በመርከብ ሆድ ውስጥ አስገብተው አንገቱን በብረት ሰንሰለት እጆቹንና እግሮቹንም እንዲሁ በብረት ማሠሪያ እንዲአሥሩት እንጀራና ውኃ እንዳይሰጡት አዘዘ እንዲዚህም ሆኖ ዐሥር ቀን ኖረ ። ከዚህም በኋላ አውጥቶ በፊቱ አቁሞ ለአማልክቶቼ ስገድ አለው እምቢ ባለውም ጊዜ ደሙ እንደ ውኃ እስቲፈስ ከባላ ግንድ ላይ አውጥተው አጥብቀው እንዲጨምቁት ሁለተኛ አዘዘ ። እንዲሁም በእርሱ ላይ አድርገው በውህኒ ቤት አሠሩት ። የእግዚአብሔር መልአክ ገብርኤልም ደግሞ ተገለጠለትና አይዞህ መልካም ገድልህን እስከምትፈጽም እኔ ከአንተ ጋራ እኖራለሁና አትፍራ አለው ። ከዚህም በኋላ ወደ እስክንድርያ ወደ ቁልቁልያኖስ መኰንን ሰደዱት እርሱም ስለ ሥራው ሁሉ መረመረውና ሕዋሳቱ ተቆራርጦ እስቲወድቅ ድረስ ይደበድቡት ዘንድ አዘዘ ። ሁለተኛም ዘይትን አፍልተው በጆሮው በአፉና በደረቱ ላይ እንዲአፈስሱ ጐኖቹንም በእሳት መብራት እንዲአቃጥሉ አዘዘ ደግሞም በእሳት የጋሉ የብረት ችንካሮችን አምጥተው በዐይኖቹ ውስጥ አደረጓቸው ። ሁለተኛም የእጆቹንና የእግሮቹን ሥሮች ሕዋሳቱንም ሁሉ እንዲነቅሉ አዘዘ ይህንንም ሁሉ አደረጉበት በዚያን ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ሕዋሳቱን ሁሉ ፈወሰው ። ከዚህም በኋላ አንጾኪያ ከተማ አደረሱትና ወደ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም አቀረቡት እርሱም በእሳት በአፈሉት በወይን በሙጫ ድፍድፍ በማቃጠል አሠቃየው ከዚያም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል አዳነው ። ዳግመኛም በአንገቱ ከባድ ደንጊያ በሰንሰለት አሥረው ወደ ባሕርም አንከባለው ግማሽ ሥጋውን እንዲአሠጥሙ ግማሹን ግን እንዳያሠጥሙ አዘዘ እነርሱም በባሕሩ ዳር ታላቅ ምሰሶ ተከሉ በዚያም እንዳዘዛቸው አድርገው አሥረው ተውት በዚህ ሥቃይም ከቀኑ እስከ ሰባት ሰዓት ዋለ ያን ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ፈትቶ አወጣው እንደ ቀድሞውም ጤነኛ አደረገው ንጉሡም አይቶ አደነቀ ሰያፊውንም ፈጥኖ አንገቱን እንዲቆርጥ አዘዘው ያን ጊዜም አንገቱን ቆርጦ በባሕርዳር ከምድር ላይ ጣለው ሥጋውንም አንሥቶ ከቁርበት በተሠራ ጋን ውስጥ ጨመረው ሥጋውም ከራሱ ጋራ ተገናኘና እንዳልተቆረጠ ሆነ ጋኑም በሃያ ቀን እስክንድርያ እስከሚደርስ ድረስ ሰው ሳይሸከመው ብቻውን የሚጓዝ ሆነ ። የቦሀ ሀገርሰዎችም በሰሙ ጊዜ መጡ ተሸክመውም በቦሀ አገር ከአለው ቤቱ ውስጥ አስገብተው ከወንድሙ ጴጥሮስ ጋራ ቀበሩት ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ዕለት ደግሞ ቅዱስ ቢፋሞን ምስክር ሆነ ። ይህ ቅዱስ ለዮሐንስ ዘሐራቅሊ የእናቱ ወንድም ልጅ ነበር ዮሐንስም ታሥሮ ሳለ ያገለግለው ነበር ። ዮሐንስም ገድሉን በፈጸመ ጊዜ ሥጋውን ገነዘ በበድኑ ላይም እንዲህ ብሎ አለቀሰ ከእግዚአብሔር የተለየሁ ሁኜ ብቻዬን እንዴት ትተወኛለህ ከቅዱስ ዮሐንስ ሥጋም እንዲህ የሚል ቃል ወጣ ወዳጄ ቢፋሞን ከእኔ ጋራ መኖርን ከፈለግህ ፈጥነህ ወደ መኰንኑ ሒደህ ክብር ይግባውና በክርስቶስ ታመን ነገም ወደ እኔ ትመጣለህ ። ይህንንም ሰምቶ የዮሐንስን ሥጋውን ቀበረ ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ሔደ ። ክብርይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እየታመነ የረከሱ ጣዖታቱን ሰደበ ። መኰንኑም ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጠ የምስክርነትንም አክሊል ተቀበለ ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ዕለት ደግሞ የመርቆሬዎስና የመቃርስ የይስሐቅና የዕብሎን የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው ። የአብላርዮስም የምስክርነቱ መታሰቢያ ነው ። እግዚአብሔርበጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን ። በዚች ዕለት ደግሞ ቅዱስ መቃርስ ምስጋና ይግባውና በጌታችን ስም በባሕር ውስጥ በመስጠም አረፈ ። በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ዕለት ሃይማኖቷ የጸና ምግባርዋም የቀና ክርስቶስ ያደረባት የመነኰሳዪት የቅድስት ማርታ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው በስደት ሳለችም አረፈችና በተራራ ውስጥ ተቀበረች በረከቷ ከእኛ ጋር ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን ። ሰኔ 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1. ቅዱስ አባ ብሶይ ኃያሉ ሰማዕት ፪.ቅድስት ማርታ ለባሲተ ክርስቶስ በቅድስናዋ የተወደሰች: በስደት ያረፈች እናት ናት ፫.ቅዱስ ያዕቆብ ምሥራቃዊ ፬.ቅዱስ ቢፋሞን ሰማዕት ፭.ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት ፮.ቅዱስ መርቆሬዎስና ማሕበሩ ሰማዕታት ወርኀዊ በዓላት ፩, ጴጥሮስና ጳውሎስ ፪, አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብጹዐን ናቸው ። መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና ። ማቴ 5÷10 @swromariyamgedam @yekidusantarik @kesishenokweldemariam2240

የሰኔ 17 ሥንክሳር #አባ ለትጹን #ገሪማ ገረምከነ#አባ ጰላሞን #ቅዱሳን ጻድቃን#እንኳን ሰው እፅዋት የታዘዙለት አባት

ኦሪየንታልና ምሥራቅ ኦርቶዶክስ (ተከታታይ ትምህርት) ረ/ፕሮ/ ቀሲስ ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል

“በጄትና በድሮን ማጥፋት”፣ “የነጌታቸው አማፂዎችና ኤርትራ"፣ አዲስ አበባና አንቀፅ-39፣ "400 ወታደሮች ከድተዋል"፣ እጅ የሰጡት ላይ እርምጃ| EF

የሰኔ 2 ሥንክሳር#የመጥምቁ ዮሐንስ እና ነቢይ ኤልሳ ፍልሰተ አፅማቸው #ቅዱስ ታዴዎስ #ጻድቁ ኢዮብ

DAVID & GOLIATH | FULL MOVIE "NO ONE DARED" | 다윗과 골리앗 풀무비

መታሰቢያ ለሰኔ 15 ሰማዕታት - የዶ/ር አምባቸውና የጀኔራል ሰዓረ ግዲያ ተሳታፊዎችና ግቦች - “እዳትይዙት...ግደሉት" አብይ

ንአበ ነፍስና ክንገሩ ዘይብሎም ነገራት....? ብመምህር ኣስመላሽ ገብረ ሕይወት

የሰኔ 10 ሥንክሳር#ቅድስት ቤተክርስቲያን #ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ#ዋርስኖፋ እና አውሎጊስ ሰማዕታት#ቅዱስ መስቀል

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስዕሏ ስር ይህን አድርጉ ሀሳባችሁ ይሳካል ፣ አባ ገብረኪዳን

የኩርድ ህዝቦች ሙሉ ታሪክ | The entire history of Kurdistan

የማያዳግም መልስ // ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ? // ጥያቄና መልስ ክፍል 02

🔴ጻድቁ አቡነ ሐራ ድንግል 🔵የሰኔ 11 የአቡነ ሐራ ድንግል ገድል 🛑abune hara dingl gedil #orthodox #shorts

🔴 ክረምቱ ሳይመጣ ፈጥነህ ና || ለቤተ ክርስቲያን ችግር መፍትሔ | ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ |Aba Gebrekidan New Sibket 2026

የሰኔ 6 ሥንክሳር#አባ ቴዎድሮስ ሰማዕትና ገዳማዊ#40 ሰማዕታት#መነኮስ ገ/ክርስቶስ#አንተናእኔ አንቺስ ደማችንን ለማን አፈሰስን

God Says:"TAKE THIS MESSAGE SERIOUSLY, BECAUSE ONLY YOU ARE SEEING IT"/God Message Now/God Message

#new🔴ስለ ጽድቅ መሰደድ በረከቱ ምንድን ነው? ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርት || ረዳት ፕሮፌሰር ዳንኤል ሰይፈ ||#kendil_media #ቀንዲል_ሚዲያ

የሐዋርያት ሥራ ሙሉ ታሪክ - ክፍል 1 - መባዕ ቲቪ (Meba TV)

ቃየን ከየት አምጥቶ ሚስት አገባ? | መጽሐፍ ቅዱስ 66ቱ ብቻ ለሚሉ ጥያቄ | መምህር ዘበነ ለማ

አትጨነቁ|| እጅግ ጥዑም ስብከት || በርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረኪዳን ግርማ Aba Gebrekidan Girma New sibket

