የሰኔ 19 ሥንክሳር#ሐዲስ ጊዎርጊስ ሰማዕት#በአንበሳ ጀርባ የበረረ አባት#አባ ቢሶይ አኖብ #የጠራ ወርቅ#5 ጭፍሮች ሰማዕታት

የሰኔ 19 ሥንክሳር አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ዐሥራ ዘጠኝ በዚች ቀን ሐዲስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ሆነ ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም መዛሕዝም ነው ትርጓሜውም ድንገተኛ ማለት ነው ። እርሱም እስላም ነበር ከግብጽ ደቡብ ድምራ ከሚባል አገር ክርስቲያን ሴት አግብቶ ከእርሷም ሦስት ልጆችን ወለደ ከሦስቱም አንዱ ይህ ቅዱስ ነው ። ከእናቱም ጋራ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሔድ ነበር ቅዱስ ቍርባንንም ይቀበል ዘንድ እናቱን ለመናት እርሷም ማንም የክርስትናን ጥምቀት ሳይጠመቅና ንጹሕ ሳይሆን ቍርባን ሊቀበል አይችልም አለችው ። ከዚህ በኋላም ከተረፈ መሥዋዕቱ ሰጠችው በጎረሳትም ጊዜ ጣዕሟ በአፉ ውስጥ እንደ ማር ሆነ የዚች የቁራሿ ጣዕም በአፌ ውስጥ እንዲህ የሆነ የዋናው የቍርባኑ ኅብስት ጣዕም ምን ያህል ይሆን ብሎ በልቡ አሰበ ከዚያች ጊዜ ጀምሮ ክርስቲያን ይሆን ዘንድ ወደደ ። በአደገም ጊዜ ክርስቲያን ሴት አገባ ክርስቲያን ይሆን ዘንድ መፈለጉንም ነገራት እርሷም ወደ ሌላ ሀገር ሒዶ የክርስትናን ጥምቀት እንዲጠመቅ መከረችው እርሱም ወደ ሌላ አገር ሔዶ ተጠመቀ ስሙንም ለውጦ ጊዮርጊስ ተባለ ። እስላሞችም በአዩት ጊዜ ይዘው ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት ከዚያም አምልጦ ላፍጥ ወደሚባል አገር ሸሸ በዚያም ሦስት ዓመት ኖረ ። ወሬውም በተገለጠ ጊዜ ቀጡር ወደ ሚባል አገር ሒዶ የልዳዊው ሰማዕት የቅዱስ ጊዮርጊስን ቤተ ክርስቲያን እያገለገለ ኖረ ። ከዚህም በኋላ ወደ ሀገሩ ድምራ ተመለሰ እስላሞችም ሰሙ ይዘውም ለመኰንኑ ሰጡት የመኰንኑም ሚስት ክርስቲያን ነበረች ለመኰንኑም አታሠቃየው አለችው መኰንኑም አሥሮ በወህኒ ቤት ዘጋበት ። እስላሞችም ተሰበሰቡ የወህኒ ቤቱንም ደጅ ሰብረው ታላቅ ግርፋት ገረፉት አካላቱንም ቆራርጠው በሕይወትና በሞት መካከል ጣሉት ። ሲነጋም ክርስቲያኖች የሞተ መስሏቸዋልና ሊቀብሩት መጡ ነገር ግን በሕይወት አገኙት ። ከዚህም በኋላ እስላሞች ተሰብስበው ከዚህ ምክርህ ካልተመለስክ እኛ ጽኑ ሥቃይአሠቃይተን እንገድልሃለን አሉት የመዛሕዝም ልጅ የከበረ ጊዮርጊስም ሰማይና ምድርን የፈጠረ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም የፈለጋችሁትን አድርጉ አላቸው ። እጅግም ተቆጡ በመርከብ ምሰሶ ላይም ሰቅለው ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት መኰንኑም ከስቅላት አውርደው በእሥር ቤት እንዲአሥሩት አዘዘ እንደዚሁም አደረጉ ። ሚስቱም ታጽናናውና እንዲታገሥ ታደርገው ነበር ሰይጣንም እንዳያስተውና የደከመበትን ዋጋ እንዳያጣ በልቡ ወደ ክርስቶስ ያስብ ዘንድ ትመክረው ነበር ። ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጸለትና አረጋጋው አበረታታውም ከሰማዕታትም ጋራ እንደ ተቈጠረ በማግሥቱም ራሱን በሰይፍ እንደሚቆርጡት ነገረው ። በነጋም ጊዜ እስላሞች ወደ መኰንኑ ተሰብስብው ጊዮርጊስን ይሰጣቸው ዘንድ ፈለጉ መኰንኑም የወደዱትን ያደርጉበት ዘንድ እንዲሰጧቸው አዘዘ ። ከዚህም በኋላ ከእሥር ቤት አወጡት ድምራ በምትባል አገር በከበረ የመላእክት አለቃ በሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ራሱን በሰይፍ ቆረጡ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ። ከዚህ በኋላ በዚያች ቀንና በዚያች ሌሊት በሥጋው ላይ እሳትን አነደዱ እሳቱም በላዩ እየነደደ ምንም ምን አልነካውም ወስደውም በገቢያ ውስጥ ጣሉት ከዚያም አንሥተው በባሕር ውስጥ ጣሉት በእግዚአብሔርም ፈቃድ ወደ ደሴቱ ወደብ ዳርደረሰ እናቱም ጠብቃው ነበረና ወስዳ ገነዘችው ለጥቂት ወራትም በቤቷ ውስጥ ሸሸገችው ። ከዚህም በኋላ ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሠሩለት ሥጋውንም በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅና ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ተገለጡ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን ። ዳግመኛም በዚች ዕለት ሰማዕት በመሆን አባ ብሶይ አኖብ አረፈ ትርጓሜውም የጠራ ወርቅ ማለት ነው ። ይህም ቅዱስ ከድምያጥ አውራጃ ስሟ ባኖስ ከሚባል አገርከአቅራብ መኰንን ከቆጵርያኖስ ጭፍሮች ውስጥ ከከተማዋ ታላላቅ ሰዎች ልጆች ወገን ነበር ። በዚህም ቅዱስ በመኰንኑ ዘንድ ነገር ሠሩበት ። ቅዱሱም ክብርይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በፊቱ ታመነ ። ወደ አንዴናውም ወሰዱት በመኰንኑ አርያኖስም ፊት ቁሞ በጌታችን ታመነ አርያኖስም በእርሱ ላይ ተቆጣ ለአማልክትም ሠዋ አለው አልታዘዘለትም ሥቃዩንም አልፈራም መኰንኑም ወስዶ ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ከዚያም ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዘዘ ወደሚገድሉበት ቦታም ሊወስዱት አወጡት ብዙ ሕዝብም ይከተሉት ነበር እነሆ ከዚያም የአርያኖስ መኰንን አንበሶች ነበሩ ። የሚጠብቃቸውም ሰው ነበር እነርሱም በብረት ሰንሰለት ታሥረው ነበር ከእነርሱም አንዱ አንበሳ የብረት ሰንሰለቱን በጥሶ ሩጦ ወደ ቅዱሱ ደረሰ ። የእግዚአብሔርም መልአክቅዱሱን በአንበሳው ጀርባ ላይ አወጣውና ዐይነ ፀሐይ ወደሚባል አገርእስከሚያደርሰው በረረበት ቅዱሱ ግን ዐይኑን ሸፍኖ ስለ ነበረ ወዴት እንዳለ አላወቀም በዚያም ራሱን በሰይፍ ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑርለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ቀን አምስት ጭፍሮች በሰማዕትነት ሞቱ እሊህም አርሶፎኒስ፣ ጴጥሮስ፣ አስኪርዩን፣ አርጌንዮስና ቢልፍዮስ በዲዮስጲልዪስም ቅጽር ውስጥ ይኖሩ ነበር ። መኰንኑም ለጣዖታት እንዲሠዉ በአስገደዳቸው ጊዜ እኛስ የንጉሣችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ትእዛዝ እንፈጽማለን ለእርሱም እንሠዋለን አሉት መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ በአንድ ቤት ውስጥም እንዲዘጉባቸውና እስከ ሁለት ቀን እህል ውኃ እንዳይሰጧቸው አዘዘ ። ከዚያም በኋላ እንዲያመጧቸው አዘዘ በፊቱም በቆሙ ጊዜ ለአማልክት ሠዉ አላቸው እነርሱም በአንድ ቃል እኛስ ለፈጣሪያችን ለክርስቶስ እንሠዋለን ለረከሱ አጋንንት ግን አንሠዋም አሉት ። አንገታቸውንም አሥረው ወደ ሌላ አገር ይወስዱአቸው ዘንድ አዘዘ ። አርጌንዮስም ወንድሞቹን እኔ እውነትን እነግራችኋለሁ የእግዚአብሔርመልአክ አምስታችንንም በስማችን ሲጠራን ሰምቼዋለሁና አላቸው ። ዳክስ ወደሚባል መኰንንም በአደረሷቸው ጊዜ መኰንኑ አስቀድሞ አርሶፎኒስን ወስዶ ለአማልክት ሠዋ አለው እምቢ በአለውም ጊዜ በፈረስ ጅራት ላይ አሥረው በከተማ ውስጥ እንዲጐትቱትና እንዲአዞሩት አዘዘ ። በመለሱትም ጊዜ በውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ ፊቱን እንዲአጠወልጉት አዘዘ ሁለተኛም እስከ ሚጨነቅ ድረስ በሠረገላ ውስጥ አሥረው ቍልቍል ሰቀሉት ሃይማኖቱንም ጠብቆ ክብር ይግባውና ለጌታችን ነፍሱን ሰጠ ። ሁለተኛም ጴጥሮስን አቀረቡት ዳክስም ለአማልክት ሠዋ አለው ትእዛዙንም ባልተቀበለው ጊዜ እንዲአሠቃዩትና እንጨት ተክለው ዘቅዝቀው እንዲሰቅሉት አዘዘ ሁለተኛም ምድሩን ቆፍረው ከትከሻው በታች ቀብረው በቅሎዎችን በላዩ እንዲነዱበት አዘዘ ይህንንም እግዚአብሔር እየረዳው ታገሠ ከጉድጓዱም በእወጡት ጊዜ ከሥቃዩ ብዛት የተነሣ ሥጋው ጠወለገ መናገርም ተሣነው በግንድ ውስጥም አሥረው ጣሉት ። ከዚህም በኋላ አርጌንዮስን እቀረቡት ዳክስም ለአማልክት ሠዋ አለው እምቢ ባለውም ጊዜ እስከሚገድሉት ድረስ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ ያለ መብልና መጠጥም በተበሳ ግንድ ውስጥ አሥረው ዘቅዝቀው ሰቀሉት ። ዳግመኛም እስኪርዪንን አቀረቡት ዳክስም ለራስህ እዘን በክፉ አሟሟትም እንዳትሞት ለአማልክት ሠዋ አለው እምቢ ባለውም ጊዜ እንዲያሠቃዩት እንዲሰቅሉትና ሥጋውን እንዲሰነጥቁት አዘዘ ወታደሮችም ተረከቡትና በጽኑ ሥቃይአሠቃዩት በትዕግሥቱም በአሸነፋቸው ጊዜ ለመኰንኑ ነገሩት በረኃብና በጽምዕ ይሞት ዘንድ በግንድ ውስጥ አሥረው በባዶ ቤት እንዲዘጉበት አዘዘ እንዲሁም አደረጉበት ። ... ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ገድለኞች ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ዕለት የደብረ ቋዓት ቅዱሳን አባቶቻችን መታሰቢያ ነው ። በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። ሰኔ 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፩.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዲስ ሰማዕት ፪.አባ ብሶይ አኖብ ሰማዕት በአንበሳ ጀርባ ላይ የተቀመጠ አባት ፫.ቅዱሳን 5ቱ ጭፍሮች በብዙ ስቃይ ሰማዕት የሆኑ ባልንጀሮች ፬.አባቶቻችን የደብረ ቁዋዐት ጻድቃን ወርኀዊ በዓላት ፩.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት 2. ሰማዕቱ ቅዱስ ኤስድራስ ፫.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ ፬.አቡነ ስነ ኢየሱስ ፭.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም ስለዚሕ ወንድሞቼ ሆይ! ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ ። ልባሞች እንደመሆናችሁ እላለሁ ። በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ ። የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋርኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? . . እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን ። ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና ። 1ኛ ቆሮ 10÷14_18 ‪@yekidusantarik‬ ‪@EOTCOrthodoxChannel1‬ ‪@swromariyamgedam‬

ማርያምን ያየ  በእምባ የሚደመጥ ልብን የሚያሳርፍ ግጥም.... ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን
▶︎

ማርያምን ያየ በእምባ የሚደመጥ ልብን የሚያሳርፍ ግጥም.... ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን

የሰኔ 17 ሥንክሳር #አባ ለትጹን #ገሪማ ገረምከነ#አባ ጰላሞን #ቅዱሳን ጻድቃን#እንኳን ሰው እፅዋት የታዘዙለት አባት
▶︎

የሰኔ 17 ሥንክሳር #አባ ለትጹን #ገሪማ ገረምከነ#አባ ጰላሞን #ቅዱሳን ጻድቃን#እንኳን ሰው እፅዋት የታዘዙለት አባት

God Says:"TAKE THIS MESSAGE SERIOUSLY, BECAUSE ONLY YOU ARE SEEING IT"/God Message Now/God Message
▶︎

God Says:"TAKE THIS MESSAGE SERIOUSLY, BECAUSE ONLY YOU ARE SEEING IT"/God Message Now/God Message

👉 በጣም አጭሩ ጸሎት ⭕️ እንዲህ ከጸለያቹ የማይፈታ ችግር የለም | እጅግ ድንቅ ስብከት በፕሮፌሰሩ መነኩሴ አባ ኃይለ ገብርኤል | Orthodox Sibket
▶︎

👉 በጣም አጭሩ ጸሎት ⭕️ እንዲህ ከጸለያቹ የማይፈታ ችግር የለም | እጅግ ድንቅ ስብከት በፕሮፌሰሩ መነኩሴ አባ ኃይለ ገብርኤል | Orthodox Sibket

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስዕሏ ስር ይህን አድርጉ ሀሳባችሁ ይሳካል ፣ አባ ገብረኪዳን
▶︎

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስዕሏ ስር ይህን አድርጉ ሀሳባችሁ ይሳካል ፣ አባ ገብረኪዳን

የማያዳግም መልስ // ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ? // ጥያቄና መልስ ክፍል 02
▶︎

የማያዳግም መልስ // ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ? // ጥያቄና መልስ ክፍል 02

የሰኔ 6 ሥንክሳር#አባ ቴዎድሮስ ሰማዕትና ገዳማዊ#40 ሰማዕታት#መነኮስ ገ/ክርስቶስ#አንተናእኔ አንቺስ ደማችንን ለማን አፈሰስን
▶︎

የሰኔ 6 ሥንክሳር#አባ ቴዎድሮስ ሰማዕትና ገዳማዊ#40 ሰማዕታት#መነኮስ ገ/ክርስቶስ#አንተናእኔ አንቺስ ደማችንን ለማን አፈሰስን

200 DIOS TE DICE HOY: ESCUCHA ESTO ANTES DE DORMIR, MI VOZ TE DARÁ PAZ Y DESCANSO
▶︎

200 DIOS TE DICE HOY: ESCUCHA ESTO ANTES DE DORMIR, MI VOZ TE DARÁ PAZ Y DESCANSO

ሰኔ ጎልጎታ |  Samuel Asres| ሳሙኤል አስረስ | Ethiopia Orthodox Tewahido | 14 August 2023
▶︎

ሰኔ ጎልጎታ | Samuel Asres| ሳሙኤል አስረስ | Ethiopia Orthodox Tewahido | 14 August 2023

የሰኔ 13 ሥንክሳር#ቅዱስ ገብርኤል ለዳንኤል የተላከበት#አባ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም #ቃይናን #ማትያን#በወርቅ ሣህን የሚመገበው ዓይኑ ጠፋ
▶︎

የሰኔ 13 ሥንክሳር#ቅዱስ ገብርኤል ለዳንኤል የተላከበት#አባ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም #ቃይናን #ማትያን#በወርቅ ሣህን የሚመገበው ዓይኑ ጠፋ

መዝሙረ ዳዊት መፀለይ ጀምሩ! | ድንቅ ትምህርት በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ Aba Gebrekidan New Sibket 2026
▶︎

መዝሙረ ዳዊት መፀለይ ጀምሩ! | ድንቅ ትምህርት በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን ግርማ Aba Gebrekidan New Sibket 2026

Ethiopia እለተ እሮብ ሰኔ 17/2018 ሰበር መረጃዎች #AnchorMedia #EthiopiaNews Anchor Media FanoNews #ethionation
▶︎

Ethiopia እለተ እሮብ ሰኔ 17/2018 ሰበር መረጃዎች #AnchorMedia #EthiopiaNews Anchor Media FanoNews #ethionation

Zadnji putnik za Pariz | Misterij Herculea Poirota
▶︎

Zadnji putnik za Pariz | Misterij Herculea Poirota

የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሙሉ ታሪክ - መባዕ ቲቪ (Meba TV) ​@Meba_tv
▶︎

የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሙሉ ታሪክ - መባዕ ቲቪ (Meba TV) ​@Meba_tv

የሰኔ 9 ሥንክሳር #ታላቁ ነቢይ ሳሙኤል ዕረፍቱ #አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ #ሉክያኖስ ሰማዕት#ortodox
▶︎

የሰኔ 9 ሥንክሳር #ታላቁ ነቢይ ሳሙኤል ዕረፍቱ #አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ #ሉክያኖስ ሰማዕት#ortodox

አስቃሚዋ ያጋለጠችው ምስጢር|ቁንጮጃሪ የተባለ መንፈስ እንልክባቸዋለን | ጨዋ ወንድ ሳይቀር የምናመላልሰው ጫት ላይ በምንቀባው ድግምት ነው?
▶︎

አስቃሚዋ ያጋለጠችው ምስጢር|ቁንጮጃሪ የተባለ መንፈስ እንልክባቸዋለን | ጨዋ ወንድ ሳይቀር የምናመላልሰው ጫት ላይ በምንቀባው ድግምት ነው?

ቃየን ከየት አምጥቶ ሚስት አገባ? |  መጽሐፍ ቅዱስ 66ቱ ብቻ ለሚሉ ጥያቄ  | መምህር ዘበነ ለማ
▶︎

ቃየን ከየት አምጥቶ ሚስት አገባ? | መጽሐፍ ቅዱስ 66ቱ ብቻ ለሚሉ ጥያቄ | መምህር ዘበነ ለማ

الرقية الشرعية للشفاءمن السحروالعين والحسد حصن من الشيطان رقية البيت والاولاد بصوت القارئ سعيد حمدان
▶︎

الرقية الشرعية للشفاءمن السحروالعين والحسد حصن من الشيطان رقية البيت والاولاد بصوت القارئ سعيد حمدان

🔴 ክረምቱ ሳይመጣ ፈጥነህ ና || ለቤተ ክርስቲያን ችግር መፍትሔ | ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ |Aba Gebrekidan New Sibket 2026
▶︎

🔴 ክረምቱ ሳይመጣ ፈጥነህ ና || ለቤተ ክርስቲያን ችግር መፍትሔ | ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ |Aba Gebrekidan New Sibket 2026

ይህን መዝሙር 24 || በየቀኑ ከጸልያችሁ የማይሳካ ነገር የለም ||የምትፈልጉትን ሁሉ ለማግኘት እንዲህ ጸልዩ || መ/ር አድነው ወንድሙ @neamnmedia19
▶︎

ይህን መዝሙር 24 || በየቀኑ ከጸልያችሁ የማይሳካ ነገር የለም ||የምትፈልጉትን ሁሉ ለማግኘት እንዲህ ጸልዩ || መ/ር አድነው ወንድሙ @neamnmedia19