የጥቅምት 30 ሥንክሳር#መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ #ቅዱስ ማርቆስ#በገድል የተጠመደ ባሕታዊ አባ አብርሐም ገዳማዊ
ስንክሳር ዘወርኀ ጥቅምት 30 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥቅምት ሠላሳ በዚች ቀን መኑፍ ከሚባል አገር በገድል የተጸመደ ቅዱስ አባት ባሕታዊ አብርሃም አረፈ ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩና የሚያመልኩ ናቸው በዚህም ዓለም ገንዘብ እጅግ ባለጸጎች ነበሩ ። ይህም ቅዱስ በአደገ ጊዜ የምንኵስናን ልብስ ሊለብስ ሽቶ በላዕላይ ግብጽ ወደሚገኝ ወደ ሀገረ አክሚም በመርከብ ተጭኖ ሔደ ወደ አባ ጳኵሚስም ደረሰ እርሱም የምንኲስና ልብስን አለበሰው በገድልም በመጸመድ ሥጋውን አደከመ በአባ ጳኵሚስም ማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ሃያ ሦስት ዓመት ያህል በማገልገል ኖረ ። ከዚህም በኋላ በዋሻ ውስጥ ብቻውን ይኖር ዘንድ እንዲአሰናብተው አባ ጳኵሚስን ለመነው እርሱም ፈቀደለት ዓሣ የሚያሠግሩበትን መረብ የሚሠራ ሆነ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አንድ ሰውን አመጣለት ያም ሰው መረቡን ሽጦ ምግቡን አተርይገዛለታል የተረፈውንም ለድ-ኖች ይሰጣል የምግቡም መጠን ሁልጊዜ ማታ ማታ አንዲት እፍኝ ከጨው ጋር በውኃ የራሰ አተር ነው ። እንዲህም እየተጋደለ በዚያች ዋሻ ዐሥራ ሰባት ዓመት ኖረ ልብሱም ከገዳም ሲወጣ የለበሰው ከዘመን ርዝመት የተነሣ አርጅቶ ተበጣጠሰ ሥጋውንም በጨርቅ የሚሸፍን ሆነ ። በየሁለት ዓመትም ወደ መነኰሳቱ ገዳም በመውጣት ሥጋውንና ደሙን ተቀብሎ ወደ በዓቱ ይመለስ ነበር ። በዚያችም ዋሻ መኖር በጀመረባት ዓመት ሰይጣናት ወደ ርሱ በመምጣት ምትሐት እየሠሩ ተፈታተኑት እርሱ ግን ውሻን እንደሚአበር ሰው አበረራቸው ። ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ ያን ሕዝባዊ ሰው ልኮ የአባ ጳኵሚስን ረድእ አባ ቴዎድሮስን አስጠራው በመጣም ጊዜ ሰግዶ ሰላምታ ሰጠው እንዲጸልይለትና በጸሎቱም እንዲአስበው ለመነው ። ከዚህም በኋላ ሁለቱም በአንድነት ጸለዩ በዚያንም ጊዜ አባ አብርሃም በርከክ ብሎ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ አባ ቴዎድሮስም ወደ መነኰሳቱ ላከ እነርሱም መጥተው ከሥጋው በረከትን ተቀበሉ ሥጋውንም ወሰደው ከቅዱሳን ሥጋ ጋር በአንድነት አኖሩት ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋርትኑር ለዘላለሙ አሜን ። በዚችም ቀን የመጥምቁ ዮሐንስ ራስ የታየበት ነው ደግሞም የፋሲለደስ፣ የቢርወካይና የመርቲስ የማርስ የንጉሥ ይስሐቅ መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑርለ ዘላለሙ አሜን ። በጥቅምት ወር የሚነበብ ንባብ ደረሰ ተፈጸመ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን ። ጥቅምት ፴ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፩.ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ ፪.ቅዱስ አርስጥቦሎስ አባቱ ፫.ቅድስት ማርያም እናቱ ፬.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት ፭.አባ አብርሃም ገዳማዊ ፮ ቅዱስ ይስሐቅ ንጉሥ ፩.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት ፪.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት ፫.አባ ሣሉሲ ክቡር ጻድቅ ባስተዋለም ጊዜ እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ ማርያም ቤት መጣ ። ዼጥሮስም የደጁን መዝጊያ ባንኳኳ ጊዜ ሮዴ የሚሏት አንዲት አገልጋይ ትሰማ ዘንድ ቀረበች ፤ የዼጥሮስ ድምጽ መሆኑንም ባወቀች ጊዜ ከደስታዋ የተነሣ ደጁን አልከፈተችም ፥ ነገር ግን ወደ ውስጥ ሮጣ ዼጥሮስ በደጅ ፊት ቆሞ እንዳለ አወራች ። ሐዋ. ፲፪፥፲፪-፲፭ ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪረየ አላፈ እምአለ ተጻመድኩ ዘለፈ ለለአነበብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ እንተ ረሰይከ እግዚኦ ፀሪቀ መበለት ውኩፍ እምአለ አብኡ ብኡላን ዘተርፈ። ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን እስከ አረጋዊ ልሂቅ እምንኡስ ሕፃን ። ለዘጸሐፎ በክርታስ ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ ዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ ። ጌታ ሆይ ከብልፅግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀዪቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል ። እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ ። ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውና ያጻፈውም ከግዕዝ ወደ አማርኛ የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን ። @ዮሐንስ መጥምቅ @ቅዱስ ማርቆስ @ሰማዕታት

የሰኔ 19 ሥንክሳር#ሐዲስ ጊዎርጊስ ሰማዕት#በአንበሳ ጀርባ የበረረ አባት#አባ ቢሶይ አኖብ #የጠራ ወርቅ#5 ጭፍሮች ሰማዕታት

የቅዱስ ገብርኤል ልብን ደስ የሚያሰኙ የመዝሙር ስብስቦች #Kidus Gebriel Mezmur collection #eotc #orthodoxmezmur #habesha

የሰኔ 17 ሥንክሳር #አባ ለትጹን #ገሪማ ገረምከነ#አባ ጰላሞን #ቅዱሳን ጻድቃን#እንኳን ሰው እፅዋት የታዘዙለት አባት

Hiber Radio Daily Ethiopia News ዕለታዊ ዜና Jun 25/26, 2026

ክርስቲያን ነህን? #ምክረ አበው @mikreabewmedia

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስዕሏ ስር ይህን አድርጉ ሀሳባችሁ ይሳካል ፣ አባ ገብረኪዳን

🅾️ ድርሳነ ሚካኤል ድርሳነ ሩፋኤል ድርሳነ ገብርኤል ድርሳነ ራጉኤል ድርሳነ ሳቁኤል ድርሳነ አፍኒን የማኅበረ መላእክት ድርሳን @arone-vlog #eotc

🔴 ገድለ ገብረ መንፈስ ቅዱስ | gedle Gebre Menfes Kidus | የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታሪክ እና ገድል ነው | Gebre Menfeskidus

የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሙሉ ታሪክ - መባዕ ቲቪ (Meba TV) @Meba_tv

የኢትዮጵያ መስቀል ከሌሎች እንዴት እንደሚለይ! በአንድ መስቀል ውስጥ 3 ነገሮች! መምህር ዘበነ ለማ

የቅዱስ ገብርኤል መዝሙሮች ስብስብ - የተመረጡ የቅዱስ ገብርኤል መዝሙሮች|St.Gabriel Ethiopian Orthodox Mezmur Collection 2026

የአባ ኪሮስ አስገራሚ ታሪክ | መባዕ ቲቪ (Meba TV) @Meba_tv

መዝሙረ ዳዊት ረቡዕ - Mezmure Dawit Rebu

ገብረ _ መንፈስቅዱስ _ ተዓምር _ ገድል)) _ GEBREMENFESKIDUS _ ገብረመንፈስቅዱስ

💖POWERFUL PRAYER TO RECEIVE AN URGENT MIRACLE - SAINT ANTHONY OF PADUA🙏

የጥቅምት 29 ሥንክሳር#ልደተ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ #ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ#ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ

የማታ ፀሎት መዝሙር 3 : 22: 40: 9ዐ: 120

ስለ ትእቢት #orthodoxmezmur #ethioorthodox #abune

🔴 የንስሃ መዝሙር | ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ | yneseha mezmur | abel mekbib | yiker selalkegn new | ይቅር ስላልከኝ ነው

