የ ብሔረ ብጹዓን አጼ መልክአ ሥላሴ አንድነት ገዳም ታሪክ bihere btsuan atse melka silasie andinet gedam

ደብረ ገነት ቅዱስ ኤልያስ ደብረ ኤልያስ debre elias Ethiopian orthodox tewahdo church bihere btsuan atse melka silasie andinet gedam monestory documentory film ብሔረ ብፁዓን አፄ መልከዓ ስላሴ አንድነት ገዳም ከደብረ ኤልያስ ወረዳ ደጎልማ ቀበሌ ስራ ያለና ከደ/ኤልያስ ወረዳ ርዕሰ ከተማ በስተ ምዕራብ 35 ኪ/ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ገዳም ነው፡፡ ይህ ገዳም የተመሰረተው በ1994 ዓ/ም በአባ ኤልሳ አማካኝነት ሲሆን ገዳሙን ሊመሰርቱ የቻሉበት ምክንያትም ራዕይ ታይቷቸው ወደ ቦታቸው በመሄድ ሱባኤ ከያዙ በኋላ ነሐሴ 16 ቀን 1994 ዓ/ም እመቤታችን አመልክታቸው መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ገዳሙ የተመሰረተበት ቦታ አራት አቅጣጫዎች በሚገኙ ሳንሰለታማ ጎራዎች /ተራሮች/ የተከፈለ ሲሆን በእነዚህ አራቱ ሰንሰለታማ ጎራዎች ላይ ሰው ሆን ብሎ ያስቀመጣቸው እንጂ በተፈጥሮ የተቀመጡ የማይመስሉ የመስቀል ቅርጽ አለባቸው፡፡ ገዳሙ የተመሰረተው በደቡብ የተጥማ በምስራቅ ደጎልማ ቀበሌ በሰሜን የተምጫና በስተምዕራብ ደግሞ ሁለቱ ወንዞች ማለትም ተጥማና ተምጫ ከተገናኙበት ቦታ ከፍ ብሎ ሲሆን የሚገኝበት ቦታም ዝቅተኛ እና ለም መሬት ነው፡፡ በገዳሙ ውስጥ ይህ መረጃ እስከ ተጠናከረበት ድረስ ከ32 መነኮሳት በላይ የሚገኙ ሲሆን እናትና አባት የሌላቸው ህፃናትም ማረፊያና ማሳደጊያ ሆኗል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በገዳሙ ስር የሚተዳደሩ 3 ቤተ ክርስቲያናት የሚገኙ ሲሆን እነዚህም የስላሴ ቤተ ክርስቲያን የዩሐንስ ቤተ ክርስቲያንና የኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ናቸው፡፡ ይህ ገዳም ከመንፈሳዊ ማዕከልነቱ በተጨማሪ ቀዳሚ የልማት እንቅስቃሴ ማእከል ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ዘመናዊ የመስኖ ውሃ ግድብም በማስገባት በርካታ የገብያ እህል፣ የቅመማ ቅመም፣የፍራ ፍሬና የአትክልት ምርቶችን በማምረት ለገብያ በማቅረብ በርካታ ገቢ ያገኛል፡፡ በአጠቀላይ የብሔረ ብፁዓን አፄ መልከዓ ስላሴ አንድነት ገዳም በ3ቱ አድባራት በሚከበሩት አመታዊ በዓላት ከ30 እስከ 50 ሽህ የሚሆኑ ምዕመናን እንደሚገኙ ከገዳሙ አባቶች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ የብሔረ ብፁዓን አፄ መልከዓ ስላሴ አንድነት ገዳም በአቀማመጡ ፣በልማት እንቅስቃሴና በፈዋሽነቱ ታዋቂ የሆነ እምቅ የመስህብ ሀብት ያለው ቦታ ሲሆን ዓመታዊ ክብረ በዓሉም በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ሀምሌ7 ና ጥር7 ቀን በድምቀት ይከበራል፡፡ Debre Elias (ደብረ ኤልያስ) is one of the woredas in the Amhara Region of Ethiopia. ~-~~-~~~-~~-~ Please watch: "ዳኘ ዋለ ለብልበው dagne wale leblibew new music 2020 2012 "    • Video   List of playlists 1. ቅዳሴ ማርያም አንድምታ/kidasie Mariam:    • ቅዳሴ ማርያም አንድምታ ክፍል 1||kidase mariam andimt...   2. ስብከት በአባ ገብረ ኪዳን/sibket :    • EOTC TV ስብከት ሸክሜ ቀላል ነው በመጋቤ ሐዲስ አባ ገብረ ኪዳ...   ~-~~-~~~-~~-~