የቅዱስ ያሬድ ታሪክ/History of saint yared
ቅዱስ ያሬድ የተወለደው ሚያዝያ ፭ ቀን በ፭፻፭ ዓ.ም በአክሱም ከተማ ነው፡፡ አባቱ አብዩድ ወይም ይስሐቅ ይባላል፤ እናቱ ደግሞ ክሪስቲና ወይም ታውክልያ ትባላለች። አባቱ የአክሱም ጽዮን ቄሰ ገበዝ ነበር፡፡ የሞተው ቅዱስ ያሬድ በተወለደ በሰባት ዓመቱ ነበር፡፡ ያሬድ ሰባት ዓመት ሲሆነው አባቱ ስለ ሞቱበት እናቱ ትምህርት ቤት ለማስገባት ወደ አጎቱ መምህር ጌዲዮን ጋር ወሰደችው፡፡ አባ ጌድዮንም በአክሱም ቤተ ቀጢን (ቤተ ጉባኤ) መምህር ነበሩ፡፡ ያሬድ ያኔ በትምህርቱ የሚያሳየው ውጤት ደካማ ስለነበር ከሌሎች ሕፃናት ጋር ሊወዳደር አልቻለም፡፡ በመሆኑም ቅዱስ ያሬድ መዝሙረ ዳዊት በሚማርበት ጊዜ አጎቱ ይቆጣጠረው ነበር፡፡ ይህን መታገሥ ተስኖት ተስፋ ቆርጦ ከአክሱም ከተማ ወጥቶ ወደ እናቱ መንደር ማይኪራህ ወደ ምትባል ቦታ ሄዶ ተደበቀ፤ ያም ቦታ የቀዳማዊ ምኒልክ መቃብር ቦታ ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድም ወደ አንዲት ዛፍ ሥር ተጠግቶ ዐርፎ እያለ አንዲት ትል የዛፍ ፍሬ ለመብላት ዛፉ ላይ ለመውጣት ስድስት ጊዜ ሲወጣና ሲወርድ ከቆያ በኋላ በሰባተኛው ከዛፉ ላይ ወጥቶ የዛፉን ፍሬ ሲበላ አየ፡፡ አንድ ትል የዛፉን ፍሬ ለመመገብ ፈልጎ ወደ ላይ እየወጣና እየወደቀ ተደጋጋሚ ሙከራ ሲያደርግ ከቆየ በኋላ በሰባተኛው ጊዜ ወጥቶ ፍሬዋን ሲመገብ አይቶ ቅዱስ ያሬድም ትሉ ተስፋ ሳይቆርጥ በከፍተኛ ትጋት ከዓላማው ሳይናወጥ ከብዙ ድካምና ጥረት በኃላ ያሰበው እንደተፈጸመለት ተመልክቶ ‹‹ሰውነቴ ሆይ ግርፋትን ለምን አትታገስም፤ መከራንስ ለምን አትቀበልም›› ብሎ ሰውነቱን ከገሰጸ በኃላ ወደ መምህሩ ተመልሶ ‹‹አባቴ ሆይ ይቅርታ አድርግልኝ እንደቀድሞ አስተምረኝ›› አለው፤ ትምህርቱንም ቀጠለ፤ ጥብብም ተገለጸለት፡፡ ቅዱስ ያሬድ ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን አዘውትሮ እየሄደ ጥበብና እውቀትን እንዲገልጽለት የጌታዬ እናቱ እመቤቴ ሆይ ዓይነ ልቦናዬን ያበራልኝ ዘንድ ለምኝልኝ›› እያለ ይጸልይ ነበር፡፡ ከዚያም በአንድ ቀን መቶ ሃምሳ መዝሙረ ዳዊት፣ መኃልየ ነቢያት፣ መኃልይ መኃልየ ዘሰሎሞን እና ትርጓሜ መጻሕፍት ብሉያትና ሐዲሳትን አወቀ፡፡ በዚያ ዘመን ድምጹን ከፍ አድርጎ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት ዜማ አልነበረም፤ ቀስ ብሎ እንደ ውርድ ንባብ እያዜሙ ያመሰግኑ ነበር እንጂ፡፡ ያሬድ የስሙ ትርጓሜ ብዙ ነው ከብዙ በጥቂቱ ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፣ነዳሬ ኅቡአት ማለት ነው። የመላእክት ምሥጢራትን የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና። ያሬድ ማለት ርደት፣ወሪድ፣መውረድ ማለት ነው። ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጲያ አውርዷልና። ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው። ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው፣የማይቀምሰው የለም። ቅዱስ ያሬድ ሙራደ ቃልበተባለ ቦታ ሆኖ ድምፁን ከፍ አድርጎ ሲያዜም ንጉሱ አፄ ገብረ መስቀል ከነሰራዊቶቻቸዉ ንግስቲቱ ከነደንገ ጡሮቿ ፣መሳፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ሊቃዉንቱና ካህናቱ አየመጡ ያዳምጡ ነበር ይላሉ ርእሰ ደብር ጥዑመ ልሳን ካሣ በመጽሐፋቸዉ፡፡ , ቅዱስ ያሬድ በግእዝ፣በዕዝል በዓራራይ ዜማ ዝማሜ እየደረሰ እያለ ንጉሱ አፄ ገብረ መስቀል ተገኝተዉ ነበር፡፡በዜማዉ ተመስጠዉ አይን አይኑን እያዩ እንደ እርሱ እዘምማለሁ ብለዉ በያዙት የብረት ዘንግ ሳያዉቁት ቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ቸከሉት፡፡ ሁለቱም በተመስጦ ስለነበሩ የሆነዉን ነገር አላስተዋሉትም ነበር፡፡ ⇒ ዜማዉ አብቅቶ ሁለቱም ከተመስጧቸዉ ሲነቁ የቅዱስ ያሬድ እግር ዘንጋቸዉ ተሰክቶ ብዙ ደም ፈሶት ነበር፡፡ንጉሡም ደንግጠዉ እጅግም አዝነዉ‹‹ደምህን አፍስሻለሁና የምትፈልገዉን ማንኛዉንም ነገር ጠይቀኝ እሰጠሃለሁ››ሲሉ ቃል ገቡለት፡፡ ቅዱስ ያሬድም‹‹ይምለምነዉ አንድ ነገር አለ እርሱን ፈጽምልኝ››አላቸዉ፡፡‹‹የፈለከዉን ጠይቅ ፈቅጄልሃለሁ››አሉት፡፡እርሱም‹‹እስካሁን እግዚአብሔርበፈቀደልኝ መሰረት በዚህ ከተማ ከእርሰዎ ጋር ቆይቻለሁ፡፡ብዙ ደቀ መዛሙርትም ተክቼያለሁ፡፡ከእንግዲህ በኋላ የቀረኝን ዘመን በጸሎትና በብሕትዉና መኖር እንድችል ከከተማዉ ራቅ ወዳለ ቦታ ሔጄ ፈጣሪየን ማገልገል እፈልጋለሁ››ብሎ የንጉሱን ፈቃድ ጠየቀ፡፡ አፄ ገብረ መስቀልም የቅዱስ ያሬድን ቃል ሰማተዉ በዚያኑም በገቡለት ቃል መሰረት ፈቀዱለት፡፡ከዚያም ጉዞዉን ወደ ደቡብ አቅጣጫ ወደ ሰሜን ተራሮች አደረገ፡፡በዚያም አሁን በስሙ የታነጸዉ ቤተ ክርስቲያን ባለበት ቦታ ላይ በምናኔ ተወስኖ ፈጣሪዉን በብሕትዉና እያገለገለ ኖረ፡፡ምናኔ ደብረ ሐዊ ከተባለዉ ተራራ ላይ ብዙ ዓመታትን ካሳለፈ በኋላ በጸለምት ዋሻ በአንዱ ግንቦት 11 ቀን በ571 ዓ/ም ተሰወረ፡፡ የቅዱሱ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን

EOTC TV || ቅዱስ ያሬድ የተሰወረበት ምሥጢራዊ ቦታ | ክፍል 1 | part one

Ethiopia - “ተስፋ ቆርጠናል” ደብረጽዮን፣ ያላቋረጠው የአስመራው ምክርየኢትዮጵያ የ10 ሺ ዶላሩ ቪዛ፣ እስረኞች በአዞ ሊጠበቁ ነው

MK TV || ቅዱስ ቂርቆስ || እንደ ሌሎች ልጆች አይደለችም

Trump Booed & Embarrassed at World Cup Final, Election Speech Flops, Iran War Spirals: A Closer Look

ריאיון עם צגה מלקו - פריימריז לקראת הבחירות - ( አዲስ) - ዶ/ር ፀጋ መላኩ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ

ሁላችን ከዚህ በኃላ አባታችን ሆይ ስንጸልይ መርሳት የሌለብን አንድ እውነታ || ድንቅ ትምህርታዊ ስብከት || መቀሲስ ፕ/ር ዘበነ ለማ

Afghane ersticht Marius in Trier: „Ich habe nur geschrieben: Mein Kind, mein Kind“ | NIUS Live

ታቦቱን ከቅዱስ አገልግሎቱ ለይቶ በቅርስነት ለማቅረብ የሚደረግ ዘመቻ! መምህር ዘበነ ለማ

This Was Life Inside a Franciscan Convent in Assisi in 1226 | AI Reconstruction

የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሙሉ ታሪክ - መባዕ ቲቪ (Meba TV) @Meba_tv

ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ በእዝል ዘዘመነ ትንሣኤ

Saint Charbel: the report on the monk with 30,000 miracles!

ልብን የሚነኩ የኪዳነ ምህረት መዝሙሮች ስብስብ|non-Stop Kidane Mihret Mezmur Collection | Ethiopian Orthodox Tewahedo

When the police ask "Where are you headed?" — Say THIS one sentence

Influencers are promoting my fake disease 🦠

መስቀል በዓል በጉራጌ ይለያል

የቅዱስ ሚካኤል መዝሙራት ስብስብ - ለሚያዝያ 12 ወርሃዊ በዓል የተመረጡ | St. Michael Mezmurs 2026

የቅዱስ ሩፋኤል መዝሙሮች ስብስብ - ለሚያዝያ 13 በዓል የተመረጡ | St. Raphael Ethiopian Orthodox Mezmurs

🔴የኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ የተወሰነበት ምሥጢራዊ ቦታ!

