ሰኔ 21 በዓለ ህንጸተ ቤታ ለማርያም ወረብ| Sene 21 Wereb | በመምህር ፍሬ ስብሐት | አ.አ | መናገሻ ገነተ ጽጌ
#ሕንጸተ_ቤታ_ለማርያም #ወረብ ሰኔ 21 ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት አንዱ ነው፤ #ህንጸተ_ቤተክርስቲያን ይባላል። በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላክ እናት ስም የታነጸችው ሰኔ 20 ነው። አናጺውም ደግሞ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ቦታው #ፊልጵስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ #በእመቤታችን_ስም ነው። ጥንተ ነገሩስ (ታሪኩ) እንደምን ነው ቢሉ:- ... ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዛሙርቱን ‹‹ሑሩ ወመሐሩ ኩሎ አሕዛበ፤ አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ፡፡›› /ማቴ. 28:19/ ባላቸው ቃል መሠረት ዓለምን በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል:: የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና (ዮሐ. 6:56) አበው ሐዋርያት ቁርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን ፣ ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲህ ይከናወን ነበር:: ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኩራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቁጥር እጅጉን በዛ:: በተለይ ቅዱስ ጳውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ:: በዚህ ምክንያት መምሕራን ሕዝቡን ‹‹ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?›› ቢሏቸው ‹‹እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት እንደው የለን›› ሲሉ መለሱላቸው:: ... ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት #ጳውሎስና_በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች ‹‹ለምን አናንጽም?›› ብለው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ግን ‹‹ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም›› አለ:: (ለዚህ ነው ዛሬም ሊቀ ጳጳስ ካልፈቀደ ቤተክርስቲያን የማይታነጸው፡፡) ከዚያ ቅዱሳን ጳውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን #ለቅዱስ_ጴጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹የጌታችን ፈቃዱ መሆኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ›› ብሎ አዋጅ ነገረ:: ... በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔያቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መልአክትን አስከትሎ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ፤ እመቤታችን በቀኙ ነበረች፡፡ ሁሉንም ሐዋርያት በሩቅም በቅርብም ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም በስተምሥራቅ ከከተማ ወጣ ወዳለ ሥፍራ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ 3ቱንም ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው፡፡ ድንጋዮቹም እንደሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ፡፡ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሠጣቸው፡፡ እነርሱም እሣት እንዳየው ሰም ከእጃቸው እየለመለሙ (እየተሳቡ) ቁመቱን 24 ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ግርምት የምትሆን 3 ክፍል ያላትን #የመጀመሪያዋን_ቤተክርስቲያን #በ52_ዓ.ም #ሰኔ_20 ቀን አነጹ፡፡ ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ፤ ጌታችንም በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት፤ ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ፡፡›› ብሏቸው ዐረገ፡፡ ... በማግስቱ ሰኔ 21 ዕለት ደግሞ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላዕክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዟት ወረደ:: ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፤ አስቀድሞ ቤተክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን አሳየ:: ... ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ ‹‹አርሳይሮስ›› ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ‹‹አክዮስ›› እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: #አክዮስ ማለት በግዕዙ #ይደልዎ በአማርኛው ደግሞ #ይገባዋል_ያሥምርለት እንደ ማለት ነው:: ... ጌታችን ይህን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ:: አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ሆኖ፣ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቆመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ:: ... በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው:: ‹‹ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን አንጹ፤ ይህችን ዕለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ::›› ብሏቸው ከድንግል እናቱ ከመላዕክቱ ጋር ዐረገ:: ... #ሰኔ_ጎልጎታ፦ በሌላ በኩል ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም በዚህ ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ ላይ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤ በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሏታል:: የፊታችን እሁድ በሁሉም አቢያተ ክርስቲያናት የሚቆመውን የእናታችንን ሙሉ ሥርዓት አቅርበንላችኋል፡፡ መልካም የምስጋና ሌሊት ይሁንላችሁ!!! የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብሯ፣ ጣዕመ ፍቅሯና በረከቷ በሁላችን ላይ ይደርብን::

የሰኔ ማርያም ወረብ / ሕንጸተ ቤተ ክርስቲያን

ሰኔ 20 ሕንጸተ ቤታ:ሰኔ 21 ቅዳሴ ቤታ ለእግዝእትነ

ወረብ ዘ ሰኔ ማርያም ሰኔ 21 //በሊቀ ጠበብት መ/አእምሮ//ጻድቃኔ ማርያም ሚዲያ

ሰኔ 12 የቅዱስ ሚካኤል በዓል ወረብ | Sene Mikael Wereb | በመምህር ፍሬ ስብሐት መንገሻ | አ.አ. | መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ

ሓጺር ታሪክ ናይ ድንግል ማርያም ቅዳሴ ቤታ - Eritrean Orthdox Tewahdo Sibket - Eritrean Orhdox Tewahdo Mezmur 2022

ግንቦት 12 ቀን የአባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ክብረ በዓል ወረብ በደብረ ሊባኖስ ገዳም ሊቃውንት ሲቀርብ።

ሰነ 21 | ቅድስት ድንግል ማርያም | ንምንታይ ነኽብሮ ? | sene 21| sene mariyam

የሐምሌ 22 የቅዱስ ዑርኤል በዓል ወረብ | Hamle 22 Wereb | በመምህር ፍሬስብሐት መንገሻ | አ.አ

🔴 ክረምቱ ሳይመጣ ፈጥነህ ና || ለቤተ ክርስቲያን ችግር መፍትሔ | ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ |Aba Gebrekidan New Sibket 2026

ወረብ ዘሰኔ ማርያም/ህንጸተ ቤታ ክብረ በዓል ክፍል አንድ

#NEW🔴#ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው የዮሐንስ ወንጌል ም. ፫፥፳፱ በመምህር ዘላለም ወንድሙ @wongelezelalemmedia #ስብከት#eotc

Built To Last - Dr. Corey L. Brown

ስርዓተ ማህሌት ዘቅዳሴ ቤታ (ማርያም 21 ሰኔ) ክብረ በዓል - Mahlet Mariam Sene 2023

Ethiopia :- ሰኔ ጎልጎታ | ለምን እናከብራለን ? | ሰኔ 21 | sene 21 | sene golgolta | ጎለጎታ | ዮናስ ቲዩብ | yonas tube

የሰኔ ማርያም ሙሉ ወረብ በመምህር ልሳነ ወርቅ ሞላ

ሰኔ 20 ለምን ይከበራል?ከእምቤታችን ጋር ምን ግንኙነት አለው?መምህር ዘበነ ለማ

ሰኔ ማርያም ምልጣን Sene Mariam Miltan 2018

ወረብ ዘሐምሌ ሥላሴ Hamle Selassie Wereb

ወረብ ዘሰኔ ማርያም

