አስገራሚ የሕይወት ጉዞዎች| ያልተሰሙ አስደገናቂ አስገራሚ የደግነት ስራዎቹ (@gizemedia1974)#ethiopia#Semebalageru
አስገራሚ የሕይወት ጉዞዎች ውልደት እና የልጅነት ዘመን ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው (በቅጽል ስሙ “ሰሜ-ባላገሩ”) ከአባቱ ከአቶ በለው ሹምየ እና ከእናቱ ከወይዘሮ እናትነሽ ቢልልኝ መስከረም 17 ቀን 1960 ዓ.ም. ውብ በሆነችው፣ የአባይ እና የጣና መፍለቂያ በምትባለው ባህር ዳር ከተማ ተወለደ። ያደገውም በዚሁ ከተማ “ቀበሌ 03” (በተለምዶ አባ ፋሲሎ ትምህርት ቤት አካባቢ) በሚባለው ሰፈር ነው። ከልጅነቱ ጀምሮ ለድምፅና ለሙዚቃ ልዩ ፍቅርና ተፈጥሯዊ ተሰጥኦ የነበረው ሲሆን፣ በሰፈሩና በጓደኞቹ ዘንድ በማራኪ ድምፁ እና በደግነቱ እጅግ ይታወቅ ነበር። ገና በ14 ዓመት ታዳጊነቱ በባህር ዳር ሕጻናት ኪነት ቡድን ውስጥ በመሳተፍ የረጅም ዘመን የጥበብ ጅማሮውን መሠረት ጥሏል። ሰሜ ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን የግጥም፣ የዜማና የቲያትር ደራሲም የነበረ ሲሆን ቀልዶችንም በተፈጥሮአዊ ዘይቤ በማቅረብ ለኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብ ደምቆ የሰራ ባለሙያ ነበር። 2. የትምህርት ህይወት የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በትውልድ ከተማው በባህር ዳር ያጠናቀቀ ሲሆን በትምህርት ቤት ቆይታውም በትምህርቱ ጎን ለጎን በኪነ-ጥበብ ክበባት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ ነበር፦ • አንደኛ ደረጃ፦ በሰርፀ ድንግል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት • መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ፦ በአባ ፋሲሎ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት • ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ፦ በጣና ሃይቅ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተምሯል። 3. ወደ ሙዚቃው ዓለም መግባትና የጥበብ እድገት የሰማኸኝ የኪነ-ጥበብ ጅማሮ ከቀበሌና ከከፍተኛ ተነስቶ በወቅቱ የነበረውን የአብዮታዊት ኢትዮጵያ ወጣቶች ማህበር (አኢወማ) ክፍለ ሀገሩን እስከመወከል የደረሰ ነበር። ለሙያው ያለው ልዩ ፍቅርና ታታሪነት በብዙዎች ዘንድ ግንዛቤ በማግኘቱ፣ ህዳር 11 ቀን 1978 ዓ.ም. በወጣትነት ዕድሜው የጎጃሙ ዝነኛ የኪነት ቡድን “ግሼ አባይ” አባል ለመሆን በቃ። • የኪነት ቡድን አሻራ፦ በ"ግሼ አባይ" ውስጥ በርካታ ምርጥ ባህላዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን በተለይም ከታዋቂዎቹ ድምፃውያን ከነይሁኔ በላይ እና ከሀብቱ ንጋቱ (አንሙቴ) ጋር በመሆን ያቀረበውና ለአራት አስርተ ዓመታት ያህል በሕዝብ ልቦና ውስጥ ታትሞ የኖረው “አንቱየዋ” የተሰኘው አስደናቂ ሙዚቃዊ ድራማ በታሪኩ ትልቅ ቦታ አለው። • የሽግግር ወቅት (የአዲስ አበባ ህይወት ጅማሮ)፦ በ1982 ዓ.ም. የከተማዋና የአካባቢው የኪነ-ጥበብ ስራዎች መቀዛቀዛቸውን ተከትሎ ሰማኸኝ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከታዋቂው ታንጎ ሙዚቃ ቤት ጋር በመሆን የመጀመሪያውን የሙዚቃ አልበሙን አሳተመ። በመቀጠልም ከኤሌክትራና ከተለያዩ በዘመኑ አሉ ከተባሉ አሳታሚዎች ጋር ሰርቷል። ይህንንም ተከትሎ ኑሮውን በአዲስ አበባ አደረገ። ከዚህም በመቀጠል “ያዢኝ አላበድሁም” የሚለውንና ሌሎችንም በህዝብ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆኑ ሥራዎችን በተከታታይ ከሙያ አጋሮቹ ጋር በመሆን ለህዝብ አቅርቧል፤ ይህም ለሙያው ከፍተኛ ዝናን አጎናጥፎታል። • የምሽት ክለቦችና የካዛንችስ አሻራ፦ ከ1983 ዓ.ም. ጀምሮ በሶስና የምሽት ክበብ፣ ከ1988-1989 ዓ.ም. በአይቤክስና በሸዋ ጌጥ የምሽት ክበባት ውስጥ በድምፃዊነት ካገለገለ በኋላ፣ በ1990 ዓ.ም. በካዛንችስ የራሱ የሆነውን የባህልና ዘመናዊ ምሽት ቤት በመክፈት በወቅቱ ደክሞ የነበረውን የጥበብ ስራ እንደገና እንዲጎመራ እና እንዲያንሰራራ ለማድረግ በግሉ ለኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። • በትያትር ዘርፍ የነበረው ተሳትፎ፦ ሰሜ ከሙዚቃውም ባሻገር በትያትር ዘርፍ ባለ ሙሉ ተሰጥኦ የነበረ ሲሆን፣ በብሔራዊ ቴአትር መድረክ ላይ ከፍተኛ ህዝባዊ ተቀባይነት ያገኘነውን “የባላገር ፍቅር” የተሰኘውን ተውኔት ጨምሮ በተለያዩ ልዩ ልዩ ሙዚቃዊ እና ተውኔታዊ ሥራዎች ላይ በቅንነትና በብቃት ተሳትፏል። • የሙዚቃ ስልቱ፦ ሰማኸኝ በተለይ የጎጃም ባህላዊ ዜማዎችን (ባቲ፣ አምባሰል፣ ትዝታ እና አንቺሆዬን) በመጨመር ከዘመናዊ የሙዚቃ ስልቶች (Modern Beats) ጋር አቀናጅቶ በማቅረብ አዲስ መንገድ የቀደደ ድምፃዊ ነው። 4. ታዋቂ የሙዚቃ ስራዎቹ ሰሜ ባላገሩ በረጅም ዓመታት የጥበብ ስራዎቹ የሀገር ባህል የሙዚቃ ዘርፍን ወጉን እና ስርዓቱን ጠብቆ በከፍተኛ ደረጃ ያስተዋወቀ የጥበብ ባለውለታ ነው። ዋና ዋና አልበሞች እና ስራዎች • “ባላገር”፦ ‘ባላገር’ የሚለው ቃል በከተሜው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ‘አልሰለጠነ’ ኋላቀርነት መገለጫ በሆነበት ዘመን፣ ይህንን ተገቢ ያልሆነ ትችትና ልማድ ለመቀየር በቁጭት በመነሳት በኪነ-ጥበባዊ ዘይቤ ‘ባላገር ነኝ’ በማለት በድፍረት ሰብሮታል። በሄደበትና ሙያውን ባስተዋወቀባቸው ዓለማትና መድረኮች ሁሉ እንደ አርሶ አደር በመልበስና የመገልገያ ዕቃዎችን በማስተዋወቅ፣ እራሱ አርሶ አደሩን በመሆን ጭምር ለባላገሩ ያለውን ፍቅር በክብር አሳይቷል። የአርሶ አደሩን ውብ እሴት፣ ባህልና ወግ በአድናቆት የዘከረበት ይህ ስራው የእውቅናው ሁለተኛውና ከአንቱየዋ ሊስተካከል የሚችል መጠሪያው ሆኗል። ከዚህ በኋላም ሰማኸኝ በለው መባሉ ቀርቶ ‘ሰሜ ባላገሩ’ እየተባለ መጠራት ጀምሯል። • “ውቧ ባህር ዳር” (ዲስካው)፦ ለትውልድ ከተማው ያለውን ጥልቅ ፍቅርና ናፍቆት የገለጸበት ተወዳጅ ስራው ነው። በዚህ ሥራው ውቧን ባህር ዳር ከልጅነት መንደሩ እስከ አጠቃላይ ገፅታዋ የገለጠበት፣ ፍቅርን፣ ጨዋታን፣ የመንደሩን አኗኗር ዘይቤ፣ ቅይጥ ውበትንና በዚህ ውስጥ የትውልድ ከተማውን ለሁሉም አብሮ አደጎቹ በትዝታ አስቃኝቷል። • “ደቦት እንስራ”፦ የልጅነት ትዝታንና የገጠሩን ባህል በተለይ መስከረምን ተከትሎ ያሉትን ሃይማኖታዊ በዓላት (ከዘመን መለወጫ እስከ መስቀል) ያለውን በጣም አስደሳች እና ውብ በዓል በትዝታ ላለፍንበት የሚያስታውስ፣ ለማያውቁት ደግሞ መስከረም በመጣ ቁጥር ያለውን ውብ የፀደይ ወቅት ያሳየበት፣ መስከረምን በልዩ እንድንናፍቀው የሚያደርግ ውብ የኪነ-ጥበብ ሥራው ነው። • “ዘገኛ”፦ በጥንተ ባህላዊ ትውፊት የተቃኜውን በፈጣን ውዝዋዜ የታጀበና በዓይነቱ ውብ የሆነ፣ ወደ ህዝብ ያልወጣን ባህል ደምቆ እንዲወጣ ያደረገበት ድንቅ የአዘፋፈን ስልት ነው። ሌሎች ተወዳጅ የባህልና የትዝታ ስራዎቹ ተወዳጅ ዜማዎች ኧረ ምኑን ሰጠሽ እንቆቅልሽ አውደ ዓመት ማነሽ ማነሽ አለሽ ነገር የኔ አለም ዝናቡ አለም እንደምነሽ ተጠቃሽ ናቸው። ሰሜ ባላገሩ እነዚህንና ሌሎች ተወዳጅ ሥራዎቹን በተለያዩ ጊዜያት በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በእስራኤል እና በአረብ አገራት ለሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች ባቀረባቸው ኮንሰርቶች አገራዊ ናፍቆትን በመወጣት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል፤ ሀገራቸውን እንዳይረሱና በባህላቸው እንዲኮሩ የበኩሉን ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። #gizemedia1974 ጊዜ ሚዲያ በተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን በመጎብኘት ያልታዩ፣ ያልተሰሙ እና ያልተዳሰሱ ጉዳዮችን ወደ ህዝብ በማምጣት ለተመልካች ያደርሳል! ለቻናላችን አዲስ ከሆኑ አሁኑኑ ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን! ስራችንን ተመልክተው ከወደዱት Like ያድርጉ! ሃሳብ ወይም አስተያየት ካሎት በኮመንት ባሩ ላይ ያስቀምጡልን! የተለያዩ መረጃዎችን ለኢትዮ አዲስ መረጃ ማድረስ ከፈለጉ ወይም በስፍራው ተገኝተን እንድንዘግብልዎ የሚፈልጉት ማህበራዊ ጉዳዮች ካሉ በሀሳብ መስጫ ሳጥናችን ላይ አድራሻዎን ያስቀምጡልን!

እኔ ከሞትኩ ሌላ ሴት እንዳታገባ // ታዋቂዉ ቲክቶከር ከቤት ተባረረ

🔴የድምፃዊ ሰማኸኝ በለው ህልፈተ ህይወት መንስኤው ምንድነዉ? - | Dallol Entertainment

ራበኝ...ህመም ከመድረክ ለየው...የልጄስ ድራማ መሪ ተዋናዩ ዳኒ ፂሞን ያጋጠመዉ በሽታ ምንድነዉ ?የመጀመሪያ ቃለ-መጠይቅ በሰይፉ በኢቢኤስSeifu on EBS

ልጆቼ እናታችሁ በሕይወት አለሁ አልሞትኩም |3 ወልቼ የወላድ መኃን ሆንኩ|አሜሪካን ቴክሳስ ያላችሁ አግዙኝ(@gizemedia1974)

7 በምስጢር በፍጥነት የሚያረጁዎት የቡና ልማዶች/ 7 Coffee Habits That Secretly Age You Faster

ታዋቂው የከተማችን ፓስተር ላስጠጋሽ ብሎ በሴት ልጆቹ ፊት ደፈረ*ኝ|ክፍል 2|(@gizemedia1974)

Ethiopia - ህወሓት ስለዘመቻው ግልጽ አደረገው፣ "ከጠቅላዩ ጎን ነኝ"፣ የግብጽ ጦር ወደ ሱዳን እየገባ ነው፣ ህወሃትን የከዱት ጄኔራል

ዶክተሮቹ ምን አሉ? ትንታኔ ይዘናል-የሙያ ባልደረቦቹ ሃዘናቸውን ....#mesetoday #mese #ehtiopian#semahegn

እኔን አረብ ሀገር ልኮ ከሰራተኛዬ ጋር መማገጥ ጀመረ@gizemedia1974

Maryland 19ኛ ፎቅ ላይ በእሳት ቃጠሎ የተጎዳው ልጄን አድኑልነኝ የእናቱ የድረሱልኝ ጥሪ

አርቲስቷ ሰለ ነፃነት ወርቅነህ ያስተላለፈችው ልብ የሚነካ መልዕከት|የአርቲስቶቻችን ሳቅ እና እንባ|ኃጫሉ ይህን ቀን አይቶ በነበረ(@gizemedia1974

ያልተነገሩት የአርቲስቱ ሚስጥሮች -ገራሚ ሰው!#meseshow #abbaytv #habesha #duet

እስከ መቼ?አርቲስቶቹ በአርሲ ጉዳይ ዝምታቸው ሰበሩ!(@gizemedia1974)

ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው ሲታወስ Mengizem Media In memory of Semahagn Belew Jun 15,26

በፌስቡክ ተዋውቄ የጀመርኩት ትደር ዋጋ አስከፈለኝ! ክፍል 2 #shegerinfo #meseretbezu|Ethiopia

የበደል ጥግ ..! || ዘመኔን ዋጋ የከፈልኩላቸው ልጆቼን ..! || እጅግ ከባድ የህይወት ዋጋ የተከፈለበት @erq-media-TV

የአርቲስት ሰማኸኝ በለው የቀብር ስነስርዓት | Emotional Moments at artist Semahegn Belew Funeral Ceremony Today

“የTDF ምላሽ ስለወታደራዊ ምልመላው”፣ “ሉዓላዊነት ይደፈራል” ዐቢይ፣ ጄኔራሉና ህወሓት በአዋጁ፣ የትራምፕና ኔታንያሁ እሰጣገባ| EF

የማያልቀው የቤተሰብ ጉድ|ወንድሜን በድግመት አሳብዳው 2 ፍቅረኞች በአንዴ ያዘችበት(@gizemedia1974)

