የጨረቃ ህገ ወጥ ቤቶች እጣ ፋንታ በአዋጁ!
የጨረቃ (ህገ ወጥ) ቤቶች እና የመሬት ይዞታ እጣ ፋንታ ለምን ይፈርሳሉ? አዋጁ ከመቼ ዓ.ም ወዲህ ያሉትን ያጠቃልላል? #ኢትዮጵያ #yezare #ethiopianbroadcastingcorporation #how #news #parliamentelection በ1967 ዓ.ም. ሐምሌ 19 ከታወጀው አዋጅ በኋላ የከተማ ቦታ እና መሬት የመንግሥት ነው። በዚህ ሕግ መሠረትም አንድ ቤት ሕገ ወጥ ነው የሚባለው ያለመንግሥት ምሪት በዘፈቀደ በተያዘ መሬት ላይ የተሰራ ከሆነ ነው። ይህም በተለምዶ የጨረቃ ቤት ይባላል። መንግሥትም እነዚህ ቤቶች ላይ ወዲያውኑ እርምጃ የመውሰድ ሥልጣን አለው። ነገር ግን መንግሥት እርምጃ ሳይወስድ ቆይቶ፣ ቤቱ በመንግሥት ተመዝግቦ ግብር ሲከፈልበት ከቆየ በከፊል ሕጋዊ፣ በከፊል ሕግ ያላሟላ (ድብልቅ) እንደሚባል የሕግ ባለሙያው ያስረዳሉ። ከዚያም መብራት እና ውሃ ሲገባለት፣ የስልክ መስመር ሲዘረጋለት እና ሕጋዊ በማድረግ ሒደት ውስጥ ካርታ ሲሰጠው ሕጋዊ ቤት ይሆናል። ካርታው በመሠራት ላይ ያለ (ካዳስተር ቁጥር) የተሰጠው፣ ነገረ ግን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ያልተሰጠው በከፊል ብቻ ሳይሆን ሕጋዊ ለመሆን ብዙ ነገር ያሟላ ቤት ይባላል። ታዲያ መንግሥት የማፍረስ ሥልጣን ያለው የትኛውን ቤት ነው? አቶ ታምራት እንደሚሉት መንግሥት ሕገ ወጥ ብሎ ማፍረስ የሚችለው ያለ መንግሥት ምሪት በዘፈቀደ በተያዙ መሬቶች ላይ የተሰሩ፣ ብዙም ያልቆዩ እና ሕጋዊ ሒደት ውስጥ ያልገቡ ቤቶችን ነው። መንግሥት ዝም ብሎ ከቆየ በኋላ ድንገት ተነስቶ ቤቶቹን ማፍረስ እና ውጡ ማለት ሕጋዊ መሠረት እንደሌለው አቶ ታምራት አስረድተዋል። “ምንም ያላሟላ፣ ቀበሌም ያልመዘገበው፣ ካርታም የሌለው፣ የቤት ቁጥር ያልተሰጠው አዲስ ቤት ቢሆን እንኳ ለማፍረስ ሕጋዊ ሒደት አለው” ይላሉ ባለሙያው። የመጀመሪያው ራሳቸው ባለቤቶቹ እንዲያፈርሱ ጊዜ መስጠት ነው። በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ማፍረስ ካልቻሉ በመንግሥት ወጪ እንዲፈርስ ይደረጋል። ፍራሹም መንግሥት ጋር ይቀመጣል። ፍራሹ መንግሥት ጋር ቢቀመጥም ንብረትነቱ ግን የባለቤቶቹ ነው። ስለዚህም ቤቱን ለማፍረስ የወጣውን የመንግሥትን የጉልበት ኪሳራ ከፍለው ንብረቱን አስለቅቀው መውሰድ ይችላሉ። “አሁን ባለው ቤት ፈረሳ፣ ሕግ ያሟላል የተባለውንም ጭምር ማፍረስ እና ፍራሹንም መውሰድ አትችሉም ብሎ መከልከል በስፋት እየታየ ነው” የሚሉት የሕግ ባለሙያው፣ “ይህ ትልቅ ስህተት እና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው” ሲሉ ኮንነውታል። ሕጋዊ ሰነድ ያላቸው ቤቶችስ? አቶ ታምራት እንደሚሉት እነዚህን ቤቶች ለማፍረስ ምትክ ቦታ ማዘጋጀት ግዴታ እንደሆነ ሕጉ ያዛል። “ሕጋዊ ሰነድ ያላቸው ቤቶች መንግሥት መዝግቧቸዋል። በመመዝገቡ መንግሥትም ኃላፊነት መውሰድ አለበት። ቤቱ ሕገ ወጥ ከሆነ መጀመሪያውኑ ማስፈረስ እና ማስቆም ሲገባው ሕጋዊ አድርጎ መዝግቦ ቆይቶ፣ ብድግ ብሎ ማፍረስ ተገቢ አይደለም” ይላሉ አቶ ታምራት። በመሆኑም እነዚህን ቤቶች ወደ ሕጋዊ መንገድ ማምጣት ካልሆነ ደግሞ ካሳ ተሰጥቶ አሊያም እንደ ኮንዶሚኒየም ያሉ የመንግሥት ቤቶችን በመስጠት መስተናገድ እንዳለባቸው ይገልጻሉ። ይህ ካልሆነስ? የሕግ ባለሙያው እንደሚሉት ተበዳዮቹ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ከተሰጣቸው ቀድመው በፍርድ ቤት ክስ መስርተው ፈረሳው እንዳይካሄድ አሳግደው መከራከር ይችላሉ። “አሁን ላይ በሌሊት እና በድንገት እየሄዱ የሚያፈርሱት፣ ተበዳዮች ይህንን መብታቸውን እንዳይጠቀሙ ለማድረግ ይመስላል” የሚሉት የሕግ ባለሙያው፣ ይህም “አሰቃቂ፣ ትክክለኛ ያልሆነ፣ ሰብዓዊ መብትን የሚጻረር፣ ከሰው ልጅ የማይጠበቅና ሕገ ወጥ ድርጊት ነው” ሲሉ አውግዘውታል። ቢሆንም ግን ተበዳዮች አሁንም መፍትሔ የመጠየቅ መብት እንዳላቸው የሕግ ባለሙያው ይጠቁማሉ። በሕዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም፣ በሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እንዲሁም በፓርላማ በተቋቋሙ ሕጋዊ አካላት አማካይነት ጉዳዩ እንዲጣራላቸው የመጠየቅ መብት አላቸው። ይህም ሆኖ መፍትሔ ካላገኙ ሌላ የሕግ አማራጭ እንዳለና የአፍሪካ ሰብዓዊ መብቶች ፍርድ ቤት ድረስ ጉዳዩን በመውሰድ መጠየቅ እንደሚችሉ ባለሙያው ይመክራሉ። “ይህ መንግሥትን እና አገርን ጭምር የሚያስከስስ ነው የሚሆነው” ያሉት ባለሙያው፤ እዚህ ላይ ሳይደርስ የሚመለከተው አካል ነገሩን አስተካክሎ ፈር ማስያዝ እንደሚገባው አሳስበዋል።

በኦሮሚያ ክልል ሕገ-ወጥ የከተማ ቤትን(የጨረቃ ቤቶች) ሕጋዊ ለማድረግ የጸደቀውን ደንብ ምን ይላል? ደንቡ የማይመለከታቸው ከተሞች የትኞቹ ናቸው?

"የገጠር መሬት አዋጅ ሲታወጅ የከተማ ቤቶች አዋጅ አልታሰበም" - የትውልዶች ወግ በኢትዮጵያ ቡክ ፎረም @ArtsTvWorld

በኦሮሚያ ክልል ሕገ ወጥ ግንባታን ሥርዓት ለማስያዝ የወጣው አዲስ ደንብ | Oromia Urban Planning | Illegal Construction |

አዲስ ምዝገባ ለከተማ መሬት ባለይዞታዎች#Lawyer Mihret #ህግ #Tebeka

EMS ነገሩ በየአቅጣጫው ከፍቷል! እለታዊ የህዝብ መድረክ Sat 27Jun 2026

ህገ ወጥ የመሬት ወረራ በአዳማ ከተማ

ሰነድ አልባ ቤት እና ቦታ ላላችሁ በሙሉ ካርታ ለማግኘት እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች/መስፈርቶች ማሟላት አለባችሁ። የሕግ ባለሙያ ደመቀ ስማቸው

የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ችግርና ህገ ወጥ የቤቶች ግንባታ በጋዜጠኞች ዕይታ ክፍል 1

የመከላከያ ድል!በትግራይ ክልል እገዳ ተጣለ!

EMS Hahu መንግስትና ሃይማኖት፤ የቤተክርስቲያን ጥቃት ለምን ከዮናስ ዘውዴ ጋር የተደረገ ቆይታ 24 Jun 2026

የኢትዮጵያ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ትልሞች፤ ወደ መዋቅራዊ ሽግግር መግቢያ

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከ2005 ዓ.ም በፊት ለተሰሩና ሕጋዊ የባለቤትነት ማረጋጋጫ ለሌላቸው 13 ሺህ ቤቶች ካርታ ሊሰጥ ነው

በሱሉልታ መኖሪያ ቤቶች ያለአግባብ መፍረሳቸውን ነዋሪዎች አስታወቁ

አቶ ጌታቸው ረዳ ስለኤርትራ እና የቀድሞው ሕወሃት ምን አሉ? @ethiopiannewsagency

Building an AI-Ready Ethiopia | Myriam Said, Digital Advisor at the Office of the Prime Minister

የከተማ መሬት ይዞታና መሬት ነክ ንብረት ምዝገባ አዋጅ ETV | EBC | EBCDOTSTREAM

"ኢትዮጵያ ማንም የሚንዳት የጨረቃ ቤት አይደለችም" NEWS - ዜና @Arts Tv World

Ethiopia - “ዘመቻው ተከፍቶባኛል” ኤርትራ፣ ኢሳያስ ቤት ሀዘን ገባ፣ የደብረፅዮን ውሳኔ ተላለፈ፣ የመቀሌው ጉዞ ተሰረዘ

Panama – England Highlights | Gruppe L, FIFA WM 2026 | sportstudio

